Quantcast
Channel: Patriot Ginbot 7
Viewing all 39 articles
Browse latest View live

በህወሓት አገዛዝ እየተሰቃዩ ላሉ ወገኖቻችን ደህንነት የሚደረገው ዓለም አቀፍ ጫና ይቀጥል!

$
0
0

def-thumbከሣምንት በፊት የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን የሚመለከት አንድ መግለጫ አውጥቷል። በዚህ መግለጫው፣ አንዳርጋቸው ጽጌ ለአንድ ዓመት ሙሉ መሠረታዊ የሆኑ የታሳሪዎች መብት እንኳን ተነፍጎት ባልታወቀ እስር ቤት የሚገኝ መሆኑ እና በእንግሊዝ ባለሥልጣናትና በቤተሰቦቻቸው እንዲጠየቅ፣ ቋሚ የቆንስላና የህግ ምክር እንዲያገኝ በተደጋጋሚ የቀረበው ጥያቄ በወያኔ አገዛዝ ውድቅ መደረጉ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው መልካም ግንኙነት የሚያሻክር መሆኑ ከወትሮው ጠንከር ባሉ ቃላት ገልጿል። አዲስ አበባ የሚገኘው የብሪታኒያ አምባሳደርም እንደዚሁ ከተለመደው ዲፕሎማሲያዊ ለስላሳነት ወጣ ያለ ያለ መግለጫ አዲስ አበባ ውስጥ ለሚታተመው ሪፓርተር ጋዜጣ ሰጥቷል። እነዚህ የሰሞኑ የእንግሊዝ መንግሥት መግለጫዎች በቀና የሚታዩ ቢሆንም የብሪታኒያ መንግሥት ማድረግ ይገባው ከነበረው እና ማድረግ ከሚችለው አንፃር ሲታይ ብዙ ይቀረዋል። የአውሮፓ ኅብረት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በተደጋጋሚ አንስቷል። የተባበሩት መንግሥታትም የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝ ጉዳይ ምርመራ እንዲደረግበት እንቅስቃሴ ጀምሯል። ከላይ የተዘረዘሩት ኩነቶች፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለሟቋረጥ የሚያደርጉት ውትወታ ውጤት እያመጣ መሆኑ ያሳያል። ይህ ጥረት ለወደፊቱም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።

በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አስልጥኖ አሰማርቷችኋል” ተብለው እንደተለመደው በሀሰት የተከሰሱ ወገኖቻችን “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ መከላከያ ምስክር እንዲሆኑን ይታዘዝልን“ ብለው ሲጠይቁ ዳኛ ተብየው “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ ሰውን በመከላከያ ምስክርነት ማቅረብ ይከብዳል” ብሎ ሲናገር ተደምጧል። አቶ አንዳርጋቸው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ ብይን ሊሰጥበት ቀጠሮ ተይዟል።

አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የነፃነት አርበኛው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእስር አያያዝ ሁኔታ ዓለም ዓቀፍ የዲፕሎማሲ አጀንዳ በሆነበት በዚህ ወቅት በህወሓት አገዛዝ በተሾመ ዳኛ “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ” መባሉ አሳሳቢ ጉዳይ አድርጎ ይመለከተዋል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የተከሳሾች፣ የአቃቤ ህጉና የዳኛው ምልልስ ለተባበሩት መንግሥታት፣ ለአውሮፓ ኅብረትና ለእንግሊዝ መንግሥት እንዲደርስ እንዲያደርጉም ያሳስባል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ብቻ ሳይሆን በህወሓት እስርቤቶችና ከእስር ቤቶች ውጭ ባልታውቁ ቦታዎች ታስረው እየተሰቃዩ የሚገኙ ወገኖቻችን ሁሉ እና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃ የሚወጣው፣ ኢትዮጵያዊያን በሚያደርጉት ሁለገብ ትግል ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ራሳችንን፣ ወገኖቻችንና አገራችን ነፃ ለማውጣት የምናደርገው ትግል ማጠናከር ግዴታችን ነው። እኛ ራሳችን እንጂ ማንም ነፃነታችንን አያጎናጽፈልንም።

ይህ እንዳለ ሆኖ ግን የህወሓትን እኩይ ተግባራት በዓለም አደባባዮች ማጋለጥ፤ የህወሓት አገዛዝን ወዳጅ ማሳጣት እና በእስር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ደህነት የሚያሻሽሉ ተጽዕኖዎችን መፍጠር እጅግ አስፈላጊ ተግባር በመሆኑ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፣ በህወሓት እጅ ለወደቁ ወገኖቻችን ድጋፍ የሚያሰሙትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ያሳስባል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!


UN demands release of British activist jailed in Ethiopia amid torture fears – The Guardian

$
0
0

The Foreign Office has pushed for consular access to Andargachew Tsige with no tangible results, since the British citizen was abducted in Ethiopia a year ago

The UN has demanded the immediate release of a Briton held on death row in Ethiopia for more than a year, an intervention that campaigners say exposes Britain’s poor diplomacy towards the case.

Experts from the UN Human Rights Council have advised Ethiopia to pay Andargachew Tsige “adequate compensation” before sending him home to London, an abrupt hardening of its position on the case at a time when Britain pursues a softly, softly approach with no tangible reward.

Yemi Hailemariam campaigns in London to demand the immediate release of her partner, British citizen Andargachew Tsege, who has been held in Ethiopia since June 2014. Photograph: Alamy

Internal Foreign Office emails, disclosed for the first time, reveal that even before Tsige was kidnapped and jailed in an unknown location in June 2014, British officials had voiced fears at “the real risk of torture if [Tsige is] returned to Ethiopia”, along with “fair trial concerns”.

An eight-page judgment from the UNHRC’s working group on arbitrary detention handed to Ethiopia suggests such fears have been realised, saying that there is “reliable evidence on a possible situation of physical abuse and mistreatment which could amount to cruel, inhuman and degrading treatment.”

Tsige, 60, a father of three from London, and known to friends as Andy, was arrested in Yemen’s main airport while in transit and forcibly removed to the Ethiopian capital, Addis Ababa.

He is prominent in Ethiopian politics, having been leader of opposition party Ginbot 7, which has called for democracy, free elections and civil rights. The government has accused him of being a terrorist and in 2009 he was tried in his absence and sentenced to death.

Foreign secretary Philip Hammond has refused to demand his urgent release, preferring to push for consular access, a request rejected by Ethiopia. Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, who lives in London with their children, has spoken to him just once by telephone since his abduction.
Advertisement

Another internal government email from the UK ambassador to Ethiopia to Laurence Robertson MP, who heads the all-party parliamentary group on Ethiopia, describes the Ethiopians as “obdurate”.

Hammond recently attempted to harden up the UK’s position on Tsige, calling for rapid progress in the case, but campaigners say this remains significantly short of what is required. Another recent Foreign Office statement made no mention of Tsige, but welcomed the “generally peaceful environment” of the recent Ethiopian elections, which saw the government locking up political opponents and journalists.

Maya Foa, head of the death penalty team at legal charity Reprieve, said: “Despite the injustices that have been – and continue to be – committed against this British national, the foreign secretary refuses to ask for Andy’s release and his return back home to his family in Britain.

“The UN is right to be taking action and demanding Andy’s immediate release from his unlawful detention. The UK’s refusal to do the same is an unacceptable abdication of responsibility to one of its citizens.”

Kevin Laue of the human rights organisation Redress, which helps torture survivors, said: “The UK government should be outraged by this behaviour and should be responding in the strongest possible terms.” A Foreign Office spokesman said: “The foreign secretary has raised this case with the Ethiopian foreign minister on 13 separate occasions, most recently on 29 April 2015. The minister for Africa raised this again on 11 June. We will continue to lobby at all levels, conveying our concern over Andargachew Tsige being detained without regular consular visits and access to a lawyer.”

Source: http://www.theguardian.com/

“ኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ የወደፊት አቅጣጫዎች” አለክሳንድሪያ ቨርጂኒያ ኢሳት ባዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ ለውይይት የቀረበ

$
0
0

ብርሃኑ ነጋ (ዶ/ር)

ለግንቦት 9 (May 9th 2015) ስብሰባ ለውይይት የቀረበ

dr-berhanu-Negaመግቢያ:
የወያኔ ሥርዓት ለሀገሪቱ የማይበጅ፤ አገሪቱን አደገኛ ችግር ውስጥ የከተተና የበለጠ ጊዜ እስካገኘ ድረስ የሚያመጣው መዘዝ ዘላቂና መውጫ የሌለው ምስቅልቅል ውስጥ አገሪቱን የሚከታት መሆኑን ብዙው ህዝብ ይገነዘባል ማለት ይቻላል:: ስለ ሕዝቡ በጥቅል እንኳን መናገር ባይቻል የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቅርብ የሚከታተሉና በተለይም በተቃዋሚ ድርጅቶች አካባቢ የሚገኙ ያገሪቱ ዜጎች በግልጽ የተረዱት ጉዳይ ነው:: በተለይ በቅርብ ጊዜ የወያኔ መንግሥት በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ የሚወሰደው የጭካኔ እርምጃ (ኦሮምያ፤ አማራ፤ አፋር፤ ሶማሊ፤ ጋምቤላ፤ ሲዳማ፤ሐረሪ፤…ወዘተ) እንዲሁም ሆን ብሎ ማህበረሰቡን በዘውግ ከፋፍሎ ለማባላት የሚያደርገውን መሰሪ እንቅስቃሴ በቅርብ የሚመለከቱ በዘውግ የተደራጁ የፖለቲካ ሀይሎች ሳይቀር የወያኔ አካሄድ ለነሱም የማይበጃቸው መሆኑን በመገንዘብ የስርዓቱ እድሜ ማጠር እንዳለበት ያምናሉ፤ ምንም እንኳን ይህንን ችግር በዘውግ መሰረት ላይ የቆመ ፖለቲካ የፈጠረው መዋቅራዊ ችግር አድርገው ሳይሆን የወያኔ የተለየ አምባገነናዊ ባህርይ የፈጠረው ችግር አድርገው የሚመለከቱት ቢሆንም:: በዚህ ጉዳይ ላይ በርዕዮተ ዓለም ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አደረጃጀትና እንቅስቃሴን በሚመርጡና የሀገሪቱን ፖለቲካ በዘውግ መነጽር በሚያዩ ኃይሎች መሀከል ያለው ሰፊና መትከላዊ ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ የወያኔ ሥርዓት በቶሎ መቀየር እንዳለበት ሰፊ ሀገራዊ ስምምነት አለ ማለት ይቻላል::

ሌላው ሰፊ ስምምነት ያለ የሚመስለው ደግሞ በጥቅሉ የወያኔን ሥርዓት የሚተካው ምን አይነት ሥርዓት መሆን አለበት? የሚለው ላይ ነው:: ይህ ስምምነት “ጥቅል” ነው የሚባለው ሁሉም ምትኩ ሥርዓት “ዴሞክራሲያዊ” መሆን አለበት በሚለው ላይ ከመስማማቱ ባሻገር ይህ “ዴሞክራሲያዊ” ሥርዓት በኢትዮጵያ ሁኔታ ዘላቂና የተረጋጋ ማህበረሰብን ለመፍጠር ምን ተጨባጭ መልክ ይይዛል? በሚለው ዝርዝር ላይ ስምምነት አለመኖሩን ለማመላከትና ይህ ዝርዝር ጉዳይ ደግሞ በተግባራዊ ሂደት ላይ ወሳኝ ሚና ሊጫወት እንደሚችል ለማሳየት ነው:: ለምሳሌ ያክል ከላይ የተጠቀሰው: ፖለቲካው ዘውጌ መሰረት እንዲኖረው በሚፈልጉ ኃይሎችና ከዚያ ይልቅ በርዕዮተ ዓለም ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ እንዲኖር በሚፈልጉት መሀከል ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚይዘውን ተጨባጭ ቅርጽ በሚመለከት ያላቸው ልዩነት ትልቅ ትርጉም ያለውና በጥንቃቄ ካልተያዘ በጣም አወዛጋቢ ሊሆን የሚችል ልዩነት ነው:: ከስሜት የጸዳ፤እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለዘላቂው መመስረትን ማዕከል ያደረገ ጠንካራ ውይይት የሚፈልግ ጉዳይ ነው:: ያም ሆኖ ግን የሚፈጠረው ሥርዓት ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን እነኝህን ኃይሎች አቻችሎ ይዞ መሄድ ሊኖርበት እንደሚችል መገመትና ይህም አይነት ማቻቻል በተጨባጭ ምን መልክ ይይዛል የሚለውን በጥንቃቄ ማሰብ ብልህነት ብቻ ሳይሆን ተጨባጭ ፖለቲካ ውስጥ ከሚሳተፉ ኃይሎች የሚጠበቅ ነው:: ይህ ጉዳይ እራሱን የቻለ ውይይት የሚፈልግ ስለሆነ ወደፊት በሰፊውና ዝርዝር ተግባራዊ እንድምታው ላይ በማተኮር እንመለስበታለን:: ለዚህ ውይይት ያክል ግን ከሽግግሩ ጋር በተያያዘ አንድ አስፈላጊ ጉዳይ ላይ ብቻ እናተኩራለን:: የሽግግሩ ተዓማኒነት ጉዳይ ላይ::

የወያኔ ሥርዓት በቶሎ መወገድ አለበት፤ ይህንንም ሥርዓት መተካት ያለበት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሆን አለበት በሚሉት ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ስምምነት ካለ (በዝርዝሩ ላይ የሚኖሩት ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው)፤ ወዲያውኑ የሚነሳው ጥያቄ ደግሞ ታዲያ ይህን ሰፊ ስምምነት የሚያንጸባርቅ፤ ቢያንስ ይህን እምነት በኦፊሴል በሚያንጸባርቁ የፖለቲካ ኃይሎች ዘንድ ሰፊ ሀገራዊ የትግል መድረክ ለማዘጋጀትና በጋራ ለመታገል ለምን አስቸጋሪ ሆነ? በጋራ መታገል ባይቻል እንኳን እርስ በርስ መጠላለፉን ማስቆም ለምን አልተቻለም? የሚለው ጥያቄ ነው:: እዚህ ጉዳይ ላይ በሰፊው ሳንገባ ብዙ ጊዜ የሚቀርቡት ምክንያቶች የሚከተሉትን ይመስላሉ፤

በዘውጌ ፖለቲካ ዙሪያ በተደራጁና በሀገራዊ (ርእዮተ አለማዊ) አመለካከት ዙሪያ በተደረጁት መሀከል ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በመፍጠር ዙሪያ ያሉ የተለያዩ አመለካከቶች የፈጠሯቸው ያለመተማመን (አንዱ ሌላውን በእውነት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መፈጠር የሚታገል መሆኑን መጠራጠር)፤
የሀገሪቱ የፖለቲካ ታሪክ ሁሌም በጉልበት ያሸነፈው አካል ፖለቲካውን በኃይል የሚቆጣጠርበት ታሪክ መሆኑና ይህም ያመጣው ያለመተማመንና የመሽቀዳደም ስሜት: (በምንም መልክ የፖለቲካ ሥልጣንን የያዘው ኃይል ከዚያ በኋላ ለሁሉም የተደላደለ የመወዳደሪያ ሜዳ ይፈጥራል ብሎ ባለማመን) ሥርዓቱ በዘላቂነት የሚመሰረትበትን መንገድ ከማሰብ ይልቅ መጀመሪያ ሥልጣን ላይ ማን ይወጣል በሚለው ላይ ያጠነጠነ መሆኑ::
የፖለቲካ ሥልጣን እያንዳንዱ ድርጅት በሕዝብ ዘንድ ባለው ተቀባይነት ወይንም ትግሉን ከዳር ለማድረስ በሚያደርገው አስተዋጽኦ መሰረት የሚደላደል (ስለዚህም በእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወይንም የስራ አስተዋጽኦንና ክህሎትን ባማከለ ፍትሀዊ ክፍፍል) ሳይሆን ቢበዛ የፖለቲካ ኃይሎች የድርድር ውጤት ወይንም የጊዜው የኃይል አሰላለፍ ውጤት ነው ብሎ ከማመን የመጣ ሁሉም የራሱን ድርጅት አቁሞ ከሌሎች ጋር “በእኩልነት” ተደራድሮ እኩል የሚደለደል አድርጎ መገመት ያመጣው የድርጅቶች እንደአሸን መፍላት፤ይህ ደግሞ በበኩሉ የፈጠረው ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ሌላውን አልፎ እንዳይወጣ በተቻለ መጠን የመከላከልና የማሰናከል አባዜ…ወዘተ

እነኝህንና ሌሎች መሰል ምክንያቶችን ደምረንና ቀንሰን ስናያቸው የሚያጠነጥኑት በሁለት አይነት አለመተማመኖች ላይ ነው:: የመጀመሪያው አለመተማመን ድርጅቶቹ (ከራስ ድርጅት በስተቀር) በእርግጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ይፈልጋሉ ወይ? የሚለው መጠራጠር ሲሆን ሁለተኛውና የተያያዘው ደግሞ ባመለካከት ደረጃ ይህ ፍላጎት ቢኖራቸው እንኳን ባንድ አጋጣሚ የፖለቲካ ሥልጣንን ካገኙት በኋላ ለሁሉም እኩልና የተደላደለ ሜዳ የመፍጠር ፍላጎት ይኖራቸዋል ወይ? ያገኙትን ሥልጣን ውድድሩን አላግባብ ለማሸነፍ እንዲያስችላቸው ለራሳቸው በሚያደላ መልኩ ይጠቀሙበታል የሚለው ፍርሀት ነው:: እነኝህ ፍርሀቶች ምንም መሰረት የሌላቸው አይደሉም:: ከላይ እንደተጠቀሰው በታሪካችን የታየው ይህ ብቻ መሆኑ፤ በከፍተኛ ጥርጣሬ የተተበተበው ባህላችንና እያደር ያገዛዝ ስርዓቶች እያኮሰመኑት የሄዱት ማህበራዊ እሴታችን ሲታከልበት እንዲህ አይነት መጠራጠርና ፍርሃት ባይኖር ነበር የሚገርመው:: ስለዚህ ሂደቱ ያንን ፍርሃት በተጨባጭና አሳማኝ በሆነ መልኩ የሚቀርፍ መሆን ይገባዋል:: ከዚያም ባሻገር ግን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መፈጠሩን ዋና አላማቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱና እነኝህ ፍርሀቶቻቸው ይህ ሥርዓት እንዳይፈጠር እንቅፋት ይሆናል ብለው ከልብ የሚያምኑ የዴሞክራሲ ወገንተኞች ያሉትን ያክል፤ እነሱ ሥልጣኑን እስካልያዙ ድረስ የሚኖረውን ምንም አይነት ውጤት (ሂደቱ ምንም ያክል አመርቂ ቢሆን) ኢዴሞክራሲያዊ ነው ብለው ከማጣጣል የማይመለሱ፤ ዴሞክራሲን ላፋቸው ያክል የሚናገሩት እንጂ ከልባቸው የማያምኑበት፤ የዴሞክራሲ ሳይሆን የስልጣን ወገንተኞችም በሰፊው የሚርመሰመሱበት የፖለቲካ ምህዳር ስለሆነ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደቱ ጠንካራ መሰረት እስከሚይዝ ድረስ እነኝህን ጥርጣሬዎች የሚቀርፍ፤ የሀገራችንን የተወሳሰበ የፖለቲካ ትርምስ ከግምት ያስገባ የሽግግር ሂደት ማሰብ በጣም አስፈላጊ ነው:: ይህን ስናስብ ግን ሁሉም ሰው የሚስማማበት ሂደት ይኖራል ከሚል የዋህነት አይደለም:: ከላይ እንደተጠቀሰው የስልጣን ተካፋይ አልሆንንም ብለው እስካሰቡ ድረስ (ለምሳሌ በምርጫ ማሸነፍ ስለማይችሉ) ምንም አይነት ሂደትን የሚያጣጥሉ ይኖራሉ:: የዚህ ሂደት ተዓማኒነት በጣም የሚያስፈልገው እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ወገንተኞችን (ማለትም በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የህዝብ ውክልና ያገኘን የፖለቲካ ቡድን ማህበራዊ ተቀባይነት ወይንም ሌጂትመሲ ለመቀበል የማያቅማሙ) የሚያስማማ ሂደት እስከሆነ ድረስና ይህም በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው እስከሆነ ድረስ አመርቂ ሂደት ነው ብለን ልንወስደው እንችላለን::

ስለዚህ ሽግግሩን በተመለከተ እነኝህን ጥርጣሬዎች ሊቀርፍ የሚችልና ከሽግግሩ በኋላ በምርጫ የሚፈጠረውን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሙሉ ተዓማኒነት የሚያጎናጽፍ ሂደት ማሰብ ይገባናል:: ይህ ደግሞ ሶስት ደረጃዎች ያሉት ሂደት ነው:: የመጀመሪያው በሽግግሩ ወቅት የሚመሰረተውን “የሽግግር መንግሥት” ምንነት የሚወስነውና ይህ መንግሥት የህዝብ ውክልና ያለው መንግሥት እስከሚመሰረት ድረስ የሚሰራቸውን ስራዎች የሚመለከተው ነው:: ሁለተኛውና በጣም ወሳኙ ጉዳይ ደግሞ ከሽግግሩ ወቅት ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግረውን የመጀመሪያውን ምርጫ ተዓማኒነት የሚመለከተው ነው:: ሶስተኛው ደግሞ ከሽግግሩ በኋላ የሚኖረው ሥርዓት ቅርጽን የሚመለከት ነው:: በነኝህ ጉዳዮች ላይ ግልጽ አመለካከትና አልፎም ሰፋ ያለ የፖለቲካ ሀይሎች ስምምነት መፍጠር ከተቻለ ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚደረገውን ረጅም ጉዞና በዚህም መሰረት ዘላቂና የተረጋጋ ማህበረሰብ ለመፍጠር ያለንን እድል በእጅጉ ያሰፋልናል:: እነኝህ ሶስቱም የሽግግሩ አካሎች በጣም አስፈላጊ ቢሆኑም ለዚህ ውይይት የመጀመሪያውን ክፍል በሚመለከት ያሉትን ሥራዎች (የሽግግሩ ሥርዓት እንዴት ይቋቋማልና ምን ምን ሥራዎችን ያከናውናል የሚለውን) ለግንዛቤ ያክል ብቻ አስቀምጠን ለዚህ ውይይት በሁለተኛው ጉዳይ (የመጀመሪያውን ምርጫ በሚመለከት) እና በሶስተኛው ጉዳይ ማለትም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ቅርጽ በእኔ እምነት ለምን ፕሬዜዳንታዊ መሆኑ እንደሚያስፈልግ ላይ በማተኮር አንዳንድ ለውይይት መተንኮሻ የሚሆን የመፍትሄ ሀሳብ እጠቁማለሁ:: ይህን የመፍትሄ ሀሳብ የማቀርበው በግሌ እንጂ በድርጅቱ የጸደቀ አመለካከት አይደለም:: ሀሳቡ ግን ሰፋ ያለ ማህበራዊ ተቀባይነት፤ በተለይም ደግሞ በዴሞክራሲያዊ ምሁራንና የፖለቲካ ሀይሎች ዘንድ ተቀባይነት ካገኘ ድርጅቱ ባለው አሰራር መሰረት ወደፊት የድርጅቱ ቋሚ ፖሊሲ አድርጎ ሊወስደው፤ ከዚያም ከሌሎች የፖለቲካ ድርጅቶችና ከመላው ማህበረሰቡ ጋር ሊወያይበትና የጋራ አቋም እንዲሆን ሊሰራበት ይችላል:: ለአሁኑ ግን እንደ አንድ “የህዝባዊ ምሁር” ሀሳብ ብቻ ተደርጎ ይወሰድ::

የሽግግር ሥርዓቱ አፈጣጠርና የሚሰራቸው ሥራዎች

የሽግግር ሥርዓት የሚባለው አሁን ያለው ሥርዓት ወድቆ የህዝብ ሙሉ ውክልና ያገኘ፤ በነጻና ፍትሃዊ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እስከሚመሰረት ድረስ ያለውን አጭር ጊዜ የሚመለከት ነው:: ይህ ጊዜ በመሰረቱ አዲሱን ሥርዓት ለመፍጠር ዝግጅት የሚደረግበት ጊዜ ነው:: የሽግግሩ ሥርዓት በራሱ ምንም የሕዝብ ውክልና የለውም:: አፈጣጠሩም በአብዛኛው ያለፈው ሥርዓት የወደቀበት ሂደት የሚወስነው ነው:: ለምሳሌ የወያኔ ሥርዓት የሚሄድበት አካሄድ እንደማያዋጣው አውቆና በጉልበት ተገፍቶ ከወደቀ የሚደርስበትን ኪሳራ በመፍራት ይህንን ክፍያ ለመቀነስ በሚል በሀገሪቱ ካሉ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር በመደራደር የሚፈጠር የሽግግር ሂደት ከሆነ የሚይዘው ቅርጽና በሂደቱም የሚሳተፉ ሃይሎች አይነት፤ ወያኔ በጉልበት በሚፋለሙት ሀይሎች ተሸንፎ ወይንም በጠንካራ ህዝባዊ እምቢተኛነት ተገፍቶ ቢወድቅ ከሚፈጠረው የሽግግር ቅርጽና የሚሳተፉት ሃይሎች አይነት ይለያል:: ይህም ሆኖ ግን ሽግግሩ በርግጥም ወደ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚደረግ ሽግግር ከሆነ በዚያ አጭር ጊዜ መሰራት ያለባቸው ቁምነገሮች በደንብ የታወቁ ናቸው:: በዚህም ምክንያት የሽግግሩ ሥርዓት ስኬት ባብዛኛው የሚለካው በሽግግሩ ውስጥ ምን አይነት ሃይሎች ናቸው የተሳተፉት በሚለው ሳይሆን (በምንም መልኩ ቢሰላ በዚህ የሽግግር ሂደት ውስጥ አልተሳተፍኩም ወይንም የሚገባኘን ሚና አልተጫወትኩም ብሎ የሚያምን የፖለቲካ ወይንም ማህበራዊ ሀይል መኖሩ የማይቀር በመሆኑ) እነኝህን ስራዎች በብቃትና የአዲስ ሥርዓት ምስረታ ዝግጅቱን ተአማኒና ሰፊ ማህበራዊ ተቀባይነት ባለው መልኩ በመስራቱ ላይ ነው:: ስለዚህ በዚህ ጽሁፍ ትኩረት የምናደርገው የሚሰሩት ስራዎች ላይ ነው:: ይህ ማለት ግን በሽግግሩ ሂደት ባሉት የሥልጣን እርከኖች የሚሳተፉት ሃይሎች ማንነትና አወቃቀሩ ምንም ትርጉም የለውም ለማለት አይደለም:: በተቻለ መጠን በሽግግሩ ወቅት የሥልጣን አወቃቀር ላይ ሰፊ የፖለቲካ ሃይሎችና ማህበራዊ ስብስቦች የሚሳተፉበት መሆኑ የሽግግሩን ወቅት ስራ የበለጠ ተዓማኒ የማድረግ እድል አለው:: ሽግግሩን የማቆም ታሪካዊ እድል ያገኙ ኃይሎች ይህን አጥብቀው ሊያስቡበት ይገባል:: ዋናው ትኩረት መሰጠት ያለበት ግን የሚሰሩትን ሥራዎችና የሚፈጠሩትን ተቋማት በርግጥም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር ሁኔታውን የሚያመቻቹ መሆኑን ማስረገጡ ላይ ነው::

1) በሽግግሩ ወቅት (ሙሉውን ጊዜ) በጊዜያዊው መንግሥት የሚሰሩ ሥራዎች

ከላይ በጥቅሉ እንደተጠቀሰው በሽግግሩ ጊዜ በዋናነት የሚሰራው አዲሱን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማዋለድ የሚሰራው ስራ ነው:: ይህ ማለት በዚህ ወቅት ምንም አዘቦታዊ (routine) የመንግሥት ሥራዎች አይሰሩም ማለት አይደለም:: በጉዳዩ ላይ ብዙ ያሰቡበት ተመራማሪዎች እንደሚስማሙበት በዚህ ወቅት በማህበረሰቡ ላይ ዘላቂ ውጤት ያለው የመንግሥት ፖሊሲ ነክ ስራ ሳይሆን በተቻለ መጠን ውጤታቸው ከሽግግሩ ጊዜ የማያልፍ ስራዎች ይሰራሉ:: በዚህ ዝርዝር ላይ ክርክር ሊኖር ቢችልም ይህ እጅግ አወዛጋቢ ስላልሆነ ብዙ ትኩረት የሚያሻው ስራ አይደለም:: ይልቁንም ትኩረት የሚያሻው አዲሱን ሥርዓት በማዋለድ ሂደት ላይ ዘላቂ እንድምታ የሚኖራቸው ጉዳዮች ላይ ስለሆነ እነሱ ላይ እናተኩር:: እነኝህ ስራዎችም በራሳቸው እርስ በርስ የተገናኙ ግን ለመረዳት እንዲመች በሁለት ከፍለን ልናያቸው የሚገቡ ስራዎች አሉ:: እነኝህም የመጀመሪያው በሽግግሩ ወቅት መሰራት ያለባቸው ለቋሚው ሥርዓት መሰረት የሚሆኑ መሰረታዊ ስምምነቶችና ተቋማት ናቸው:: ሁለተኛው ደግሞ በሽግግሩ ወቅት ማህበረሰቡን ለቋሚው ሥርዓት የሚያዘጋጁና የማህበረሰቡን ስነልቦና የሚቀርጹ ተቋማትና ስነልቦናዊ ድባብ የመፍጠሩ ስራ ነው:: እነኝህ ሁሉም ስራዎች ግን ባንድ መልኩ ወይንም በሌላ ከላይ የጠቀስኳቸውን የጥርጣሬና ያለመተማመን መንፈስ የሚሰብሩ መሆን ይገባቸዋል::

ሀ) ለቋሚው ሥርዓት የማእዘን ድንጋይ የሚሆኑ መሰረታዊ ስምምነቶችና ተቋማት

እዚህ ላይ በመጀመሪያና በዋናነት የሚጠቀሰው የቋሚውን ሥርዓት የጫወታ ሕግ የሚያስቀምጠው የሕጎቹ ሁሉ የበላይ የሆነው ሕገ መንግሥት ነው:: ይህ ሰነድ ወሳኝ የሆነውን ያክል በተለይ አሁን በኢትዮጵያ ያሉ የፖለቲካ ሃይሎችን ሁሉ በሚያስማማ መልኩ መቅረጹ (ወይንም ያለውን ማሻሻሉ) በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው:: ከምክንያታዊነት ይልቅ ስሜት፤ የዛሬንና የነገን ከማሰብ ይልቅ ባለፈው ታሪክ ላይ በመንጠልጠል ደጋፊዎችን በሲቃ ስሜት (passion) ማሰባሰብን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ልሂቃን በሚርመሰመሱበት የፖለቲካ ምህዳር፤ በረጅሙ አማትሮ የሚያይ፤ ሰፋ ያለ ማህበራዊ ስምምነት ያዘለ ሕገ መንግሥት ማዘጋጀት እጅግ ከባድና የረጅም ጊዜ ራዕይን መሬት ከረገጠ የሰጥቶ መቀበል ፖለቲካ ጋር አዋህደው መጓዝ የሚችሉ አዲስ ስርዓት አዋላጅ ዜጎችን የሚፈልግ አስቸጋሪ ስራ ነው:: ይህ ሕገ መንግሥት ምን መምሰል አለበት የሚለው ጉዳይ ላይ እዚህ ጽሁፍ ውስጥ በሰፊው አልገባበትም ግን በጥንቃቄ መሰራት ያለበት፤ በፍጹም ልንተወው የማንችለው የሽግግሩ ዋና የቤት ስራ መሆኑን ጠቅሶ ማለፍ ይበቃል:::: ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንድ ወሳኝና የሚያስፈልገውን የመተማመን ስሜት በመፍጠር በኩል ጠቃሚ ነው በሚለው ጉዳይ ላይ ግን ያለኝን አመለካከት ባጭሩ እሄድበታለሁ:: ባጠቃላይ በአካሄድ ደረጃ ሊባል የሚችለው ግን ይህ ውይይት የሽግግሩ ጽንስ ከመጀመሩ በፊት ጀምሮ በሕገ መንግሥቱ ላይ ያለመስማማት ምንጭ ሊሆኑ ይችላሉ በሚባሉት ጉዳዮች ላይ ምሁራንና የፖለቲካ ልሂቃን ካሁኑ ውይይት ቢጀምሩበት ጠቃሚ መሆኑን ነው:: ሌላው በሂደት ደረጃ የሚነሳውና እጅግ አስፈላጊ የሆነው፤ ሕገ መንግሥቱን የማዘጋጀት ሂደት ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ማህበረሰቡን በሙሉ በስፋት ማሳተፍ የሚችልና ቀጣይነት ያለው ነጻ ውይይት በማህበረሰቡ ውስጥ በመገናኛ ብዙሀን አማካኝነትም ሆነ በስብሰባዎች መካሄድ እንዳለበት አጽንኦት መስጠቱ ተገቢ ነው:: የዚህን ሂደት ከባድነት ስንገልጽ ግን የሚኖሩት ልዩነቶች ጠንካራ ስሜቶች የሚንጸባረቁባቸው ቢሆኑም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረትን ማዕከል እስካደረጉ ድረስ ከሚያለያዩት ጉዳዮች የሚያስማሙት የሚበልጡ መሆናቸውን ማወቅና ማመንም ተገቢ ነው::

ከተለያዩ የአህጉራችን ተመክሮዎች እንዳየነውና የወያኔ ዘመን ፖለቲካ ማንንም በማያሞኝ መልኩ ግልጽ ያደረገው አንድ ነገር ቢኖር ሕገ መንግሥት በጹሁፍ ደረጃ መኖሩና ተግባራዊ መሆኑ ፍጹም የማይገናኙ ክስተቶች መሆናቸውን ነው:: ከዚህ አንጻር ጥሩ ሕገ መንግሥት መጻፍ በጣም ቀላሉ ነገር ነው::[1] ከላይ ሕገ መንግሥትን በማርቀቅና የማሕበረሰቡን ስምምነት እንዲያገኝ ማድረግ አስቸጋሪ ነው ያልነው በእርግጥ በተግባር የመተርጎም ፍላጎቱ አለ ብለን እስካመንን ድረስ ብቻ ነው:: ይህንን ካመንን ከባዱ የሽግግር ዘመን ሥራ የሚዘጋጀውን ሕገ መንግሥት በእውነት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልጉትን የመንግሥት ተቋማት የመፍጠርና እነኝህ ተቋማት በሕገመንግሥቱ የተሰጣቸውን ስራ ለመስራታቸው በቀናኢነት የሚጠብቁ ባለሟሎችንና ዜጎችን በመንግሥት ውስጥም ሆነ ከመንግሥት ውጭ በብዛት ማፍራት ነው:: ከዚህ አንጻር ሕገ መንግሥቱ የሚይዘው ቅርጽ ላይ ያሉ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የግድ የሚላቸውና በትክክል እንዲሰራ በጣም አስፈላጊ የሆነው የሥልጣን ክፍፍል ላይ በማተኮር በነጻነት እንዲሰሩ በጠንካራ መሰረት ላይ መቆም ያለባቸውን ዋና ዋና ተቋማት መዘርዘር እንችላለን:: ከነኝህም ውስጥ ዋናዋናዎቹ:

ፍርድ ቤቶችና ከዚያ ጋር የተያያዙ የፍትህ ተቋማት (ፖሊስ፤ የአቃቤ ሕግ መስሪያ ቤት…ወዘተ)

የመከላከያና የደሕንነት አካላት ከፖለቲካ ወገንተኛነት ተላቀው ሙያዊ ስራቸውን ብቻ እንዲሰሩ ማድረግ

ከምርጫ ጋር የተያያዘ ስራ የሚሰሩ መስሪያቤቶችን ሁሉ በተግባር ገለልተኛ ማድረግ (ይህ ጉዳይ በተለይ ከሽግግሩ ጋር የተያያዘ ስለሆነ በመፍትሄ ሀሳቡ ላይ በድጋሚ እንመለስበታለን)
በመንግሥት ባጀት የሚተዳደሩ የመገናኛ ብዙሀን ከስራ አስፈጻሚ አካሉ ነጻ በሆነ አካል ስር እንዲተዳደሩ ማድረግ
በመንግሥት ባጀት የሚተዳደሩ የትምህርት ተቋማት፤ በተለይም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የአካዳሚ ነጻነታቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲሰሩ ከስራ አስፈጻሚ አካሉ ነጻ ሆነው በቻርተር እንዲተዳደሩ ማድረግ…ወዘተ.
እነኝህና መሰል ተቋማት አዲስ የሚፈጠሩ ሳይሆኑ አሁንም ያሉ ናቸው:: አሁን የሚሰራበትንም ሕገ መንግሥት በመርገጥ ሁሉም የገዢው ፓርቲ እንደፈለገ የሚጫወትባቸው ያገዛዝ መሳሪያ ሆኑ እንጂ:: መሰረታዊ አወቃቀራቸው በሚቀረጸው ሕገ መንግሥት የሚገለጽ ቢሆንም በሽግግሩ ወቅትም የሚሰሩ ናቸው:: ስለዚህ በሽግግሩ ጊዜ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በሚመጥን መልኩ በተግባር እንዲሰሩ የማድረጉ ሀላፊነት የሽግግር መንግሥቱ ነው:: የሽግግር ሂደቱ ተዓማኒነት ከሚለካባቸው መስፈርቶች አንዱና ምናልባትም ዋናው በነኝህ ተቋማት ላይ በሚያደርገው ማሻሻል ስለሆነ የሽግግር መንግሥቱ ትልቅ ስራው አድርጎ የሚወስደው ነው::

በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ሊነሱ የሚችሉ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሳልገባ ግን ከሚፈጠረው ሥርዓት ቅርጽ ጋር በተያያዘ (ይዘቱ ዴሞክራሲያዊ መሆኑ ላይ ስምምነት እንዳለ ተቀብዬ) በተለይ ደግሞ እንዲፈጠር አስፈላጊ ነው ያልኩት በዴሞክራሲያዊ ሀይሎች መሀል የሚኖርን መተማመን ለማጠናከርና የሚፈጠረው ሥርዓት በሂደት ጠንካራ ሀገራዊ መሰረት አንዲኖረው ስለሚረዳ ብቻ የሚፈጠረው ስርዓት ቅርጽ አሁን ካለው ፓርላሜንታዊ ሥርዓት ይልቅ ፕሬዜዳንታዊ ለምን ቢሆን እንደሚመረጥ አንድ ሁለት ሀሳቦችን ላቅርብ::

ሀ_1) ፕሬዜዳንታዊ ስርዓት በኢትዮጵያ ሁኔታ ለምን ይመረጣል?

በዚህ ጉዳይ ላይ የማቀርበው አጭር አስተያየት ንድፈ ሀሳባዊ አይደለም:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የተለያዩ ቅርጾች ቢይዝም ዴሞክራሲያዊነቱን የሚያረጋግጡት መሰረታዊ ምንነቶች ተግባራዊ እስከሆኑ ድረስ ቅርጹ በራሱ ዴሞክራሲያዊነቱን ጥያቄ ውስጥ አይከተውም:: ቅርጹን የሚወስነው ደግሞ እያንዳንዱ ሀገር ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሽግግር በሚያደርግበት ጊዜ ያለበት የራሱ ታሪካዊ፤ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጨባጭ ሁኔታ ነው:: የንድፈ ሀሳብ ጉዳይ አይደለም:: በኢትዮጵያም ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በምናደርገው ሽግግር ወቅት የምንመርጠው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ቅርጽ አሁን ሀገራችን ያለችበትን ተጨባጭ ሁኔታ በጥንቃቄ በመገምገም የትኛው ቅርጽ ነው ልንፈጥር የምንፈልገውን ሥርዓት በተሻለ መደላደል ላይ ሊያስቀምጥልን የሚችለው የሚለውን ጥያቄ በመመለስ ነው:: ምንም እንኳን የዚህ የመጨረሻ ውሳኔ በሽግግሩ ወቅት የሚረቀቀውን ሕገ መንግሥት የሚያጸድቀው ህዝብ ቢሆንም፤ በዚያ ሂደት ውስጥ የሚሳተፉ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ሀይሎችና በእውቀታቸው የማህበረሰቡን ግንዛቤ መቅረጽ የሚችሉ ምሁራን ቢያንስ የሚቀርቡትን አማራጮች ጥቅምና ጉዳት በማሳየት በኩል ትልቅ ሚና ስለሚኖራቸው ይህንን ውይይት ካሁኑ መጀመሩ ጥቅም አለው ብዬ ስለማምን ነው እዚህ ጽሁፍ ላይ ባጭሩ የማቀርበው::

ያለፉት 24 አመታት የወያኔ “የውሸት ፓርላሜንታሪ ስርዓት” ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመስረት ከምር የሚፈልጉ ሀይሎችን ሊያስተምሩ የሚገባቸው ሁለት ወሳኝ ተመክሮዎች ያሉ ይመስለኛል:: አንደኛው ሁሉም የሚያውቀው በተግባርና በንድፈ ሀሳብ መሀከል ያለው ከውቅያኖስ የሰፋ ልዩነት ነው:: ስለዴሞክራሲ መለፈፍና በተግባር ዴሞክራሲያዊ መሆን ለየቅል መሆናቸውን ያለምንም ጥርጥር በአይናችንና በኑሯችን አይተነዋል:: ሁለተኛው ትምህርት ደግሞ በንድፈ ሀሳብና በኦፊሴላዊ መዋቅር የተቀመጠን አካሄድ በተግባር ለመገርሰስ ምን ያክል ቀላል እንደሚሆንና የቅለቱ መጠን ደግሞ በስርዓቱ ቅርጽ ላይ ያሉትን ቀዳዳዎች በግልጽ ላልወጣውና ለተደበቀው እውነተኛ የፖለቲካ ሃይሎች ፍላጎት ማስፈጸሚያ ማዋል እንደሚቻል ነው:: በዚህ ሂደትም የአንድን ሥርዓት እውነተኛ ምንነት ሳይሆን ከላይ የለበሰውን የማስመሰያ ልብስ ብቻ ለማየት ለሚፈልጉ አገራዊም ሆነ ውጫዊ ሀይሎች ማማለያነት እንዴት ሊውል እንደሚችል በበቂ አይተናል:: የዚህ ክፍል ውይይት በኢትዮጵያ ሁኔታ በስልጣን ላይ የሚወጡ ኃይሎች የሚፈጠረውን መዋቅር ለጠባብ ጥቅማቸው እንዳያውሉት በትንሹም ቢሆን ለመከላከል የሥርዓቱን ቅርጽ ብዙ ቀዳዳ የሌለው እንዲሆን ለመሞከር ነው::

በተግባር በኢትዮጵያ እንደምናየው እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመፍጠር የማይፈልጉ ኃይሎች የፓርላሜንታዊ ሥርዓትን ለማዋከብ (abuse) ከሚያስችላቸው ቀዳዳ አንዱ በቂ የሆነና የተለያዩ የሥልጣን አካሎችን መዋቅራዊ በሆነ መልክ መለያየት የሚችል የሥልጣን ክፍፍል ያለመኖሩ ነው:: በዚህ ሁኔታ የፓርላማው አባሎች ሥልጣናቸውንም ሆነ ተግባራቸውን የሚያዩትና የሚለኩት ለሥልጣን ካበቃቸው ፓርቲ ጥቅም አንጻር ብቻ ስለሚሆንና ጠንካራ የሆነ ተቋማዊ ተአማኒነት (institutional loyalty) ስለማይኖራቸው ፓርቲው ለመረጠው (በቀጥታ በህዝብ ያልተመረጠ) ስራ አስፈጻሚ አካል ተገዢ የሚሆኑበትን ሁኔታ ይፈጥራል:: ይህ ደግሞ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እጅግ አስፈላጊ የሆነውን ከስልጣን ክፍፍል ጋር የሚመጣውን የጎንዮሽ ተጠሪነት (horizontal accountability) ያዳክመዋል:: በፕሬዜዳንታዊው ቅርጽ ግን የስራ አስፈጻሚው አካል በመላው ህዝብ (ስለዚህም የመላውን ህዝብ ጥቅም ወደ ማስጠበቅ)፤ የህግ አውጭው አካል ደግሞ በያካባቢው ህዝብ ምርጫ ለየብቻቸው የሚሰየሙ መሆናቸውና (ስለዚህም ተጠሪነታቸው ለመረጣቸው አካባቢ ህዝብ) በዚህም ምክንያት የሚኖረው የተጠሪነት ልዩነት ተዓማኒነቱን ይበልጥ ወደ ተቋማዊ ተዓማኒነት እንዲያደላ ያደርገዋል የሚል እምነት አለኝ:: በዚህ ሁኔታ የሥራ አስፈጻሚውን ምርጫ ያሸነፈውና የሕግ አውጭውን ምርጫ ያሸነፈው አካል የተለያዩ ሊሆኑ የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ይኖራሉ:: ይህ ሁኔታ በስራ አስፈጻሚውና በህግ አውጭው መሀከል ብዙ ንትርክ ሊያመጣና አስተዳደሩንም ሊያዳክመው ይችላል:: ይህ ግን በራሱ መጥፎ ነገር አይደለም:: ይበልጡንም በጀማሪ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ የሰጥቶ መቀበል ፖለቲካ እንዲዳብር ይረዳል የሚል እምነት አለኝ::

ሁለተኛውና በተለይ በሀገራችን ሁኔታ ይህንን ቅርጽ እጅግ አስፈላጊ የሚያደርገው ባለንበት የታሪክ ሁኔታ የተፈጠረውን በዘውጌ ማንነትና በሀገራዊ ማንነት መሀከል ያለውን በቅጡ ያልተፈታ ግጭት በሂደት አገራዊ ማንነት እያደር እየተጠናከረ እንዲሄድ ያደርገዋል የሚል እምነት አለኝ:: የሀገራዊ ማንነት መጠናከር ደግሞ ለማንኛውም የሚሰራ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ማህበረሰብ በጣም አስፈላጊ ነው:: በፓርላሜንታዊ ሥርዓት መራጮች የሚመርጡት ያካባቢያቸውን ወኪል ብቻ ነው:: ያ ወኪል ላጠቃላይ ማህበረሰቡ የሚጠቅም መሪ ነው አይደለም በሚለው ላይ መራጩ ድምጽ የለውም:: በዋናነት ተዓማኒነቱ ለመረጠው አካባቢ ማህበረሰብ ነው:: በፓርላማው የተመረጡ ሰዎች (ብዙሀኑን መቀመጫ ያገኘው ፓርቲ ወኪሎች) በሚያደርጉት የስልጣን ድርድር ወይንም ፓርቲው በሚወስነው ውሳኔ ብቻ ነው የስራ አስፈጻሚውን ስልጣን የምትረከበው:: ስለዚህም ተዓማኒነቷ ለፓርቲዋ ወይንም ፓርላማው ውስጥ ላሉት ወኪሎች ብቻ ነው:: አጠቃላይ ማህበረሰቡን በእኩልነት ለማገልገል የገባችው ቃል ወይንም እንዴት ሁሉንም ማህበረሰብ እንደምታገለግል በዝርዝር ያስቀመጠችው ፕሮግራም (ካጠቃላይ የፓርቲው ፕሮግራም ውጭ) የላትም:: የስልጣኗ መሰረትም መላው (ወይንም አብዛኛው) ህዝብ አይደለም:: ይህ ሁኔታ እንደኛ አገር የዘውጌ ማንነት በበረታበት ሁኔታ ሀገራዊ ማንነትን የሚያጠናክርበት መንገድ የለውም:: በመላው ህዝብ የተመረጠች ፕሬዜዳንት በምትኖርበት ሁኔታ ግን በመጀመሪያ ተመራጯ ለምን ሥልጣን እየተወዳደረች እንደሆነ መላው ማህበረሰብ ያውቃል:: ህዝቡ የሚመርጠውም ለዚያ ሥልጣን ብቁ ነች አይደለችም ብሎና በዚያ መስፈርት መዝኖ ነው::[2] ሁለተኛ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር በብዙሀኑ ህዝብ ለመመረጥ የተለያዩ ዘውጌ ማህበረሰቦችን ድጋፍ ይፈልጋል:: የአንድ ዘውጌ ማህበረሰብን ጥቅም ብቻ የሚያስጠብቅ ነው ከተባለ ብዙሀኑ ሊመርጠው አይችልም:: ስለዚህም ፕሬዜዳንት የመሆን ፍላጎት ያለው ሰው ሀገሪቱን ከዘውጌዎች በላይ በሆነ ማንነት የማሰባሰብ ወይም ቢያንስ ለአንድ ዘውግ የሚያደላ አይደለም ተብሎ መታመን አለበት:: የፕሬዜዳንቱን ዕጩ የሚያቀርበው ፓርቲው እንኳን ቢሆን ፓርቲው ለፕሬዜዳንትነት የሚያቀርበው ዕጩ በመላው ሕዝብ ዘንድ ኢአድሏዊ በመሆኑ የሚታወቅ መሆኑን ከግምት ማስገባት አለበት:: ይህም በፓርቲው ውስጥም እንኳን የፖለቲካ ሥልጣን ይገባኛል የሚል ታታሪነት (ambition) ያላቸው ግለሰቦች ዘውጌያዊ ስሜታቸውን እንዲሞርዱ፤ ብሎም በሀገር ደረጃ እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል:: ይህ ደግሞ ባንዴም ባይሆን በሂደት የፖለቲካ ፍላጎትና ታታሪነት ያላቸውን ሰዎች ገና ከመነሻው ከዘውግ ባሻገር እንዲያስቡ ያበረታታቸዋል የሚል እምነት አለኝ:: ይህ ደግሞ እየተጠናከረ ሲሄድ ሀገራዊ ማንነትንም እያጠናከረ ይሄዳል የሚል እምነት አለኝ::

ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የሚነሳው አንድ አስፈላጊ ጉዳይና የሥርዓቱን ቅርጽ የሚወስነው ጉዳይ ለሥራ አስፈጻሚነት የሚመረጠው ፕሬዜዳንት በምንም ሁኔታ ከ50% በላይ የሆነውን ህዝብ ይሁንታ ያገኘ መሆኑን ማረጋገጥ ነው:: እንደሚታወቀው በጀማሪ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቶች የሚታወቀው አንድ ነገር ቢኖር ሥልጣን ላይ ለመውጣት ፍላጎቱና ታታሪነቱ ያላቸው ሰዎች እጥረት አለመኖሩ ነው:: በዚህ ሁኔታ ለምርጫ በእጩነት የሚቀርቡት ሰዎች ቁጥራቸው የበዛ ሊሆን ይችላል:: የዘውግ ክፍፍሉ መስመር ይዞ ጠንካራ አገራዊ ማንነት እስከሚገነባ ድረስም ለእጩነት የሚቀርቡት ሰዎች የተወሰነ የዘውግ ድጋፍ የሚያገኙ ሊሆኑ ይችላሉ:: በዚህ ጊዜ በአንድ ዙር ምርጫ ከሌላው በዛ ያለ ድምጽ ያገኘ እጩ የሚመረጥበት ሁኔታ ካለ የብዙሀኑ ድምጽ ሳያስፈልገው ምርጫውን ባብላጫ ድምጽ ብቻ የሚያሸንፍ ሊኖር ይችላል:: ይህ ደግሞ ከላይ የጠቀስኩትን የፕሬዜዳንቱን የሀገር መሪ የመሆን ተቀባይነት በእጅጉ ያዳክመዋል፤ የዘውጌ ክፍፍሉንም የበለጠ ሊያጠናክረው ይችላል:: ስለዚህ አንዱ በግልጽ መቀመጥ ያለበት ነገር በመጀመሪያ ዙር ምርጫ 50% በላይ ያገኘ እጩ ከሌለ ከፍተኛውን ድምጽ ያገኙት ሁለት እጩዎች እንደገና ለውድድር ቀርበው ከሁለቱ ከ50% በላይ ያገኘው እጩ የሚያሸንፍበትን ሂደት መከተል ያለብን ይመስለኛል:: ይህ ባንድ በኩል ከስልጣን ፍላጎት ባሻገር ለቢሮው የሚመጥን ምንም ይህ ነው የሚባል ችሎታም ሆነ ህዝባዊ ተቀባይነት የሌላቸውን ሰዎች በምርጫው ውስጥ ገብተው የውድድሩን ሂደት መጫወቻ እንዳያደርጉት ከወዲሁ ተስፋ የሚያስቆርጣቸው ሲሆን በዋናነት ግን ከላይ እንደጠቀስኩት ያለ ብዙሀኑ ድምጽ ይሁንታ በጎንዮሽ ድርድርና አሻጥር የሚገኝ ሥልጣን እንደማይኖር ምልክት ይሰጣል::

ይህን ጉዳይ በመጠኑ ያነሳሁበት ምክንያት ግልጽ ከሆነ ይበልጥ አከራካሪ ሊሆን ስለሚችለው የመጀመሪያውን ምርጫ በሚመለከት ያለኝን ሀሳብ አቅርቤ ላጠቃልል::

ለ) በሽግግሩ ወቅት ማህበረሰቡን ለቋሚው ሥርዓት የሚያዘጋጁና የማህበረሰቡን ስነልቦናዊ ድባብ የሚያዘጋጁ ሥራዎች

ሌላውና ከመጀመሪያው ባልተናነሰ አጽንኦት ተሰጥቶት የሚሰራበት የሽግግር ወቅት ስራ በሽግግሩ ሙሉ ዘመን በማህበረሰቡ ዘንድ እንዲፈጠር የሚፈለገውን የስነ ልቦና ድባብ የሚቀርጹ ስራዎች ናቸው:: እነኝህ ስራዎች ገሚሶቹ ከላይ በተጠቀሱት ተቋማት የሚሰሩ ሲሆኑ ሌሎቹ መንግሥት በሚሰራቸው ሳይሆን በማይሰራቸው፤ ማህበረሰቡ ውስጥ በሚኖሩ ወይንም ሽግግሩን ተከትሎ እንደ አዲስ በሚፈጠሩ የማህበረሰቡ ተቋማት የሚሰሩ ናቸው:: እነኝህን ተቋማት አንድ ሁለት ብሎ ከመጥቀስ ይልቅ በማህበረሰቡ ዘንድ እንዲፈጠር የሚፈለገውን ስነ ልቦናዊ ድባብ መግለጹና ለዚህም የሚያስፈልጉትን ሁኔታዎች ማስቀመጡ ይቀላል:: ባለፉት አርባ ግድም አመታት በኢትዮጵያ ሥልጣን የጨበጡ መንግሥታት በማህበረሰቡ ላይ ከፈጠሩት አስከፊ ሁኔታዎች ውስጥ አንዱና ዋናው የማህበረሰቡን ስነ ልቦና ማኮላሸትና የሞራል መሰረቱን መናድ ነው:: ይህንን የመጠገን ሂደት መጀመር የሽግግር ወቅቱ አንድ ሥራ ነው::

ያገዛዝ ስርዓቶች ለመግዛት ከሚያስፈልጋቸው ነገር አንዱ ህብረተሰቡን በፍርሀት ቆፈን ውስጥ መክተት ነው:: እየፈሩ ስለ ሀገር የልብን መናገርና መከራከር አይቻልም:: እየፈሩ በነጻነት መምረጥ አይቻልም:: እየፈሩ የመንግሥትንና የመንግሥት ባለሟላትን ስህተቶችና ጥፋቶች ማጋለጥ አይቻልም:: በፍርሀት ማህበረሰብ ውስጥ የዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መሰረቶች መገንባት አይቻልም:: ስለዚህ በሽግግሩ ወቅት የመንግሥት (እንዲሁም ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት) አንዱ ስራው ማህበረሰቡን ከዚህ የፍርሀት ቆፈን ማላቀቅ ነው:: እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት በአብዛኛው የፍርሀት ምንጭ መንግሥት ራሱ ነው:: ማህበረሰቡን ከፍርሀት ለማላቀቅ ቆርጦና አስቦ የሚሰራ መንግሥት፤ ማህበረሰቡ መንግሥትን እንዲፈራ ለረጅም ጊዜ የደረሰበትን የስነልቦና ተጽእኖ ገፍፎ በምትኩ መንግሥት የሚፈራ ሳይሆን በስራው የሚከበርበትን ሁኔታ መፍጠር አለበት:: በዚህ ዙሪያ መንግሥት ነጻ ውይይትን የሚያበረታታበት (የመንግሥት ሚዲያን በነጻነት እንዲሰራ በማድረግ)፤ ከመንግሥት ውጪ ሀላፊነት የሚሰማቸው ነጻ የህትመትም ሆነ የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች በስፋት የሚሰራጩበትን ሁኔታ ማመቻቸት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በነጻነት ምሁራዊ ውይይቶችን እንዲያዘጋጁ ማበረታታት፤ የተለያየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው የፖለቲካ ሰዎችም ሆኑ ምሁራን እነኝህን ሚዲያዎች ተጠቅመው በሀገሪቱ ጉዳይ ላይ በድፍረት እንዲሳተፉ ማበረታታት፤ ማህበረሰቡ በያካባቢው በሀገሩ ጉዳይ ላይ ያለምንም ፍርሀት የሚሳተፍበትን ሁኔታዎች ማመቻቸት…ወዘተ በጣም አስፈላጊ ነው::

ከዚህ ጋር የተያያዘና የማህበረሰቡን ስነ ልቡና ሊያረጋጋ የሚችል ሌላ ሥራ የብሄራዊ እርቅ ሂደት ነው:: በደርግ ሥርዓትም ሆነ በወያኔ ያገዛዝ ዘመን ብዙ በጣም ብዙ ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ወንጀሎችና ግፎች ተፈጽመዋል:: ብዙ ኢትዮጵያውያን ሞተዋል፤ አካለ ስንኩላን ሆነዋል፤ ተሰደዋል ከኑሮ ተፈናቅለዋል:: እንደ ማህበረሰብ እነኝህ ኩነቶች የስነ ልቡና ጠባሳ ፈጥረዋል:: ብዙዎቹ በደሎች ገና ቁስላቸው ያላሻረ ነው:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በተረጋጋ ሁኔታ እንዲጀመር ከተፈለገና ሥርዓቱ የሚፈልገው ቀና ማህበራዊ ውይይትና ክርክር እንዲኖር ካስፈለገ ይህ ያልደረቀ ቁስል የሚያሽርበት መንገድ መፈለግ አለበት:: ይህ በተበዳዮች በኩል ትልቅ ትዕግሥት፤ ሆደ ሰፊነት፤ ይቅር ባይነት፤ በበዳዮች በኩል ደግሞ እውነተኛ ጸጸት የሚጠይቅ አስቸጋሪ ስራ ነው:: ባንድ በኩል ላለፈው ፍትህ ፍለጋ: በሌላ በኩል የወደፊቱ የመረጋጋት ፍላጎት ማህበረሰቡን ወጥረው የሚይዙት አስቸጋሪና አስጨናቂ ተግባር ነው:: ይህ በምን መልክ ይደረጋል የሚለው በራሱ የሰከነ ውይይት የሚፈልግ ነው:: ግን በሽግግሩ ወቅት መተግበር ያለበት ሥራ ነው:: ማህበረሰቡን ከፍርሃት የማላቀቅና ባዲስ መንፈስ የማስጀመሩ ስራ አንድ አካል ነው::

ማህበረሰቡን የፍርሃት ቆፈን ውስጥ የሚከተው ግን መንግሥት የሚያደርገው ድርጊት ብቻ አይደለም:: የማህበረሰቡን ሰላምና ደህንነት የሚያውኩ ከመንግሥት ውጭ ያሉ ሀይሎችም ካሉ በማህብረሰቡ ስነልቦና ላይ ተመሳሳይ ተጽእኖ አላቸው:: ስለዚህ ማህበረሰቡን ከፍርሀት ቆፈን የማላቀቅ አንዱ የሽግግሩ መንግሥት ስራ በሀገሪቱ ሰላምን ማስፈን ነው:: በሃሳብ ደረጃ የሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች ያለምንም ተጽእኖ እንዲስተናገዱ እያበረታቱ እነኝህ ክርክሮች በምንም አይነት ወደ ሀይልና “የማይስማማን አመለካከት በጉልበት የሚያፍን” ወይንም ምናልባት ለምርጫው ጊዜ ለመዘጋጀት ካሁኑ ተቀናቃኞችን የማኮላሸት አይነት አካሄድ እንዳይሻገሩ መጠበቅ በጣም ያስፈልጋል:: ይህ ብዙ ጊዜ የሚሆነው በፖለቲካ ድርጅቶችና ደጋፊዎቻቸው አካባቢ፤ በተለያዩ የሃይማኖት አክራሪ መሪዎችና ተከታዮች አካባቢ፤ የመንግሥትና የሚዲያ አይን በበቂ በሌለባቸው ቦታዎች፤ ባጠቃላይ ስሱ ስሜቶች በሚንጸባረቁባቸው ጉዳዮችና የመንግሥትን ሥልጣን ሀብት ለማካበት እንጠቀምበታለን ብለው የሚያስቡ የፖለቲካ ድዊዎች አካባቢ ስለሆነ የሽግግር መንግሥቱ የጫወታውን ሕግ ለሁሉም እኩልና ግልጽ አድርጎ ካስቀመጠና ለሕጉ ተዓማኒነቱን እራሱ በተግባር እያሳየ ለእንዲህ አይነት ግጭቶች ምንም ትዕግስት እንደሌለውና ፍጹም ተቀባይነት እንደማይኖራቸው ማሳየት አለበት:: በተቻለ መጠን የሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች ከውሸት የጸዱ፤ ምክንያታዊና የሰለጠኑ እንዲሆኑ በምሳሌነት ማሳየትና መምራት አለበት::

ፍርሃትን ከማስወገድ በተጨማሪ የማህበረሰቡን የሞራል መሰረት የመገንባት ጅማሮ (ይህ ረጅም ጊዜ የሚወስድ ሥራ መሆኑን ባለመርሳት) ታስቦበት መሰራት የሚጀምረውም በዚህ የሽግግር ወቅት ነው:: እንደሚታወቀው በተለይ በወያኔ ሥርዓት እጅጉን የተጎዳው የማህበረሰቡ የሞራል መሰረት ነው:: ሥርዓቱ የህብረተሰቡን ግብረገብነት የሚቀርጹትን የሃይማኖት ተቋማት ከማራከሱ ባሻገር፤ የማንኛውም ህብረተሰብ ሰላምና ዘላቂነት ዋስትና የሆኑትን ማህበራዊ እሴቶች ሆን ብሎ ንዷቸዋል:: ለዓብነት ያክል ሁለት ምሳሌዎችን ብቻ እንጥቀስ:: ውሸትና ሙስና:: እነኝህ ሁለት ማህበራዊ ደዌዎች በማህበረሰባችን ዘንድ ቤታቸውን ሰርተዋል ማለት ይቻላል:: ያገዛዝ ስርዓቶች አይነተኛ መገለጫ የሆኑ፤ ውጤታቸው ግን ካገዛዝ ስርዓቱ ተጠቃሚዎችም ባለፈ የማህበረሰቡን ስነልቦና ሁሉ የሚበክልና የበከለ መሆኑን መካድ አይቻልም:: ስለዚህም እነኝህን ደዌዎች ለማከም ሰፋ ያለ የህብረተሰብ ተሳትፎን የሚጠይቅ ነው:: ይህንን ስራ ግን በተግባር በማሳየት ቀዳሚውን ሚና የሚጫወተው የሽግግሩ መንግሥት ነው:: ለምሳሌ የሽግግሩ መንግሥት ማህበረሰቡን ላለመዋሸት፤ የመንግሥት ባለሟላት በምንም አይነት አውቀው ውሸት እንዳይናገሩ፤ እንዲህ አይነት አስነዋሪ ምግባር በአድራጊዎቹ ላይ ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍል ማሳየት ይችላል:: የስነ ጥበብ ባለሙያዎች የውሸትን ማህበራዊ ጉዳት በሚመለከት ማህበረሰቡን የሚያስተምሩ ብዙ የኪነት ስራዎች ሊሰሩ ይችላሉ:: ትምህርት ቤቶች ወጣቶችን በዚህ ዙሪያ ማስተማር ይችላሉ…ወዘተ. ሙስናንም በተመለከተ እንደዚሁ:: የሽግግሩ መንግሥት ከሙስና የጸዳ እንዲሆን፤ ማህበረሰቡን ሙስና “ተጎጂ የሌለበት በሽታ” (victimless) ሳይሆን ጠቅላላ ማህበረሰቡን በተለይ ግን ድሆች ዜጎችን የበለጠ የሚያጠቃ፤ የማህበረሰቡን የሞራል ህልውና፤ የፖለቲካ መረጋጋትና የሚፈጠረውን ሥርዓት ይዘት ለዘላቂው የሚበክልና ያለይቅርታና ርህራሄ መዋጋት ያለብን ተውሳክ መሆኑን ማስረዳት፤ በሙሰኞች ላይ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ እየተከታተሉ ጠንካራ እርምጃ በመውሰድ በምንም አይነት በሙስና መክበር እንደማይቻል ማሳየት ይገባል:: መንግሥት እንዲህ አይነት ቆራጥ አቋም መያዙ ሲታይ በመንግሥት ባለሟሎች ዘንድ ብቻ ሳይሆን ባጠቃላይ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረው ስነልቦና ይህንን ነቀርሳ ለዘላቂው ለማስወገድ ትልቅ እርዳታ ይሰጣል:: በተለይ ከፖለቲካ ሥልጣን የሚገኝ የኢኮኖሚ ጥቅም አለ ብለው ፖለቲካውን ራሱን ለማቆሸሽ ወደኋላ የማይሉ አድርባዮችን ለመጥረግ፤ ስለዚህም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱን በተሻለ የሞራል መደላደል ላይ ለማስቀመጥም ተጨማሪ እገዛ ያደርጋል:: እነኝህ በሽታዎች ባንድ ጊዜ ይነቀላሉ የሚል የዋህነት አይኖረንም:: ግን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲመሰረት የሚያስከፍሉት ኪሳራ ከፍተኛ መሆኑን በማሳየት በሽግግሩ ጊዜ የሚወሰዱት እርምጃዎች ለዘላቂ መፍትሄ መንገድ ይጠርጋሉ::

በሽግግሩ መንግሥት የስራ ዘመን የሚሰሩትን ስራዎች ለናሙና ያክል ካስቀመጥን የዚህ ውይይት ዋና ክፍል የሆነውንና የሽግግሩ ዘመን ማለቁንና ወደ ዘላቂው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግረንን፤ የመጀመሪያውን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በሚመለከት ያለኝን አመለካከት ከነመፍትሄው ወደሚገልጸው ክፍል እንሻገር::

የሽግግሩ ወቅት የመጨረሻና ወሳኝ ስራ፤ የመጀመሪያው ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ
የሽግግሩ መንግሥት እነኝህን ሰፋፊ ስራዎች በብቃት መስራቱ ሳያንሰው ከምንም ነገር በላይ የብቃቱና የትክክለኛነቱ መለኪያ ስራውና በርግጥም ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመሸጋገሩን እውነታ የሚያበስረው ወይንም የሚሰብረው የመጀመሪያው ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ፤ባገሪቱ ህዝብም ሆነ ባለማቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማድረጉና ስልጣንን በሰላማዊ መንገድ ለተመራጩ ማስተላለፉ ላይ ነው:: ይህ ምርጫ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ካለው ፋይዳ አኳያ ምናልባትም ሁሌም ከሚቀርቡት መፍትሄዎች ወጣ ያለና ደፋር (bold) መፍትሄ የሚፈልግ ሊሆን ይችላል:: መታወቅ ያለበት ዋናው ቁም ነገር ይህ ምርጫ እውነትም ነጻና ፍትሃዊ መሆኑ ላይ ብቻ አይደለም:: እውነተኛ የህዝብ ፍላጎት የተገለጸበት መሆኑን ምንም አይነት ጥርጣሬ እንዳይኖረው ማድረጉ ላይ ነው:: ነገሩን አስቸጋሪ የሚያደርገውም ይኸው ነው:: ከላይ እንዳልነው ማህበረሰባችን ባጠቃላይ፤ በተለይም የፖለቲካ ድርጅቶች አካባቢ ያለው ስር የሰደደ ጥርጣሬና አለመተማመን እስካለ ድረስ ሂደቱ ትክክል እንኳን ቢሆን በምርጫ በተሸነፉ ኃይሎች አካባቢ “ያላግባብ ነው የተሸነፍኩት” የሚል ስሜት (perception) መፈጠሩ የሚቀር አይመስልም:: በተለይ ደግሞ በሽግግሩ ወቅት የመንግሥት ሥልጣንን የያዘው ኃይል ምርጫውን እስካካሄደው ድረስና ይኸው ኃይል ምርጫውን ካሸነፈ የምርጫውን ሂደት ስለዚህም የሚፈጠረውን አዲስ ሥርዓት በጥርጣሬ ውስጥ ይጥለዋል:: ይህ ደግሞ ዘላቂ አደጋ ነው የሚሆነው:: ስለዚህ ይህን ምርጫ ከምንም አይነት ጥርጣሬ ነጻ ላማድረግ ምን መደረግ አለበት የሚለው ወሳኝ ጉዳይ ይሆናል::

ይህን ጥርጣሬ ፈጽሞ ለማስወገድ የሚቻለው ምርጫውን የሚያካሂደውን አካል በጊዜው ሥልጣን ላይ ካለው ኃይል ሙሉ ለሙሉ መለየት ነው:: ከዚያም በተጨማሪ ምርጫውን የሚያካሂደው ኃይል ይህን ምርጫ ለማካሄድ ብቃቱ ያለውና በሃገሪቱ ካሉት የፖለቲካ ኃይሎች ሁሉ ምንም ወገንተኛነት የሌለው መሆኑን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን ይህንንው ለሁሉም የፖለቲካ ተቀናቃኞችና ነጻ ተመልካቾች ሁሉ ማሳመን ይጠበቅበታል:: የኢትዮጵያን ፖለቲካ በቅርብ ለሚከታተል ማንም ሰው ይህ ምን ያክል ከባድና ምስጋና የሌለው ሥራ እንደሆነ መገመት አያቅትም:: ታዲያ ይህንን ስራ ማን ቢሰራው ነው የተሻለ ተዓማኒነት የሚኖረው?

ይህን ጥያቄ ለመመለስ ያሉትን አማራጮች በጥንቃቄ መመልከትና ካሉት አማራጮች ውስጥ የበለጠ ከጥርጣሬ የጸዳ ነው የሚባለውን መምረጡ ተገቢነው:: ምርጫን ነጻና ፍትሃዊ ለማድረግ እስከዛሬ ከነበሩት ተመክሮዎች ውስጥ የሚከተሉት ይጠቀሳሉ:

ሀ) በመንግሥት በተቋቋመ ነጻ የምርጫ ኮሚሽን ዋና አስፈጻሚነት የሚካሄድ (በተጨማሪ የውጭ ታዛቢዎች ትዝብታቸውን የሚገልጹበት)

ለ) የሚቋቋመው የምርጫ ኮሚሽን በሃገሪቱ ከሚገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች በእኩል ተዋጽኦ ማቋቋምና ኮሚሽኑ በምልዓተ ድምጽ የሚያሳልፈው ውሳኔ ትክክለኛ ነው ብሎ መቀበል

የመጀመሪያው አካሄድ ከሞላ ጎደል አብዛኛው ወደ ዴሞክራሲ የሚደረግ ሽግግር ተግባራዊ ያደረገው አካሄድና በኢትዮጵያም የተተገበረው ነው:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሰረት ያልጣለባቸው ሀገሮች ውስጥ ሁሌም ይህ አካሄድ በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል የሚመርጠውና በብዙ ሃገሮች ተመክሮ እንደታየው በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል እራሱን በሚጠቅም አኳኋን ሂደቱን ያጨናገፈበት ሁኔታ ነው የሚታየው:: ለዚህ ምሳሌ ከኢትዮጵያችን ውጪ ሌላ አገር መጥቀስ አያስፈልገንም:: በጣም በቅርብ የሆነ የሌላ ሃገር ምሳሌ ካስፈለገ ከሰሞኑ በግብጽ የሆነውንና በአፍጋኒስታን ባለፈው ዓመት የሆነውን ማየት ብቻ ይበቃል:: ይህ የሚሆንበት ምክንያት ደግሞ በሥልጣን ላይ ያለው ኃይል የምርጫ አስፈጻሚውን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር በማድረጉ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚታየው የምርጫ አስፈጻሚው ኃይል ተቋማዊ ደካማነት ነው:: እንዲህ አይነት ተቋም በሕግ የተሰጠውን ነጻነት ተግባራዊ ለማድረግ ሶስት ተያያዥ ሁኔታዎች ተሟልተው መገኘት አለባቸው:: በመጀመሪያ የሕግ ተቋማቱ በራሳቸው ነጻ የሆኑና የመንግሥት ስልጣን የያዘውን አካል ከሕግ በታች መሆኑን ማስረገጥ የሚችሉ መሆን አለበት:: ይህ በራሱ ትልቅ ስራ ነው:: ቀጥሎ የምርጫ አስፈጻሚው ተቋም ራሱ ለነጻነቱ ቀናኢ የሆነ፤ ከምንም ነገር በላይ ለተቋሙ ነጻነት የቆመ፤ ሥራውንም በተገቢው ለመስራት የሚችል ተቋማዊ ብቃት ያለው መሆን አለበት:: ሶስተኛው ደግሞ በተቋሙ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፤ በተለይ በሃላፊነት ላይ ያሉት ሰዎች፤ ከፍተኛ ሙያዊ ብቃት ያላቸው ብቻ ሳይሆን ሙያው የሚጠይቀው ጠንካራ መንፈስና የሞራል ልዕልና ያላቸው ሰዎች መሆን አለባቸው:: እንዲህ አይነት ተቋም እንዲኖር ደግሞ በሽግግር ወቅት ሥልጣን ላይ ያለው ኃይል የምር ፍላጎቱ ቢኖረው እንኳን፤ እንደ ኢትዮጵያ በፍርሃት ቆፈን ውስጥ ለረጅም ጊዜ ከቆየ ማህበረሰብ፤ ለዚህ የሚመጥን ክህሎትና ድፍረቱ ያላቸው ባለሙያዎች በአጭር የሽግግር ወቅት ይገኛሉ ማለት አስቸጋሪ ነው:: በሽግግሩ ባለስልጣናት የሚሾሙት የምርጫ ኮሚሽን አባላት ገና በቂ የሥራ ልምድና ተቋማዊ ነጻነት ባላዳበሩበት ሁኔታ የውጭ ታዛቢዎች መኖራቸው ይህንን ሁኔታ ሊቀይረው አይችልም:: የምርጫ ታዛቢዎች ምርጫው እንከን የለሽ ነው ቢሉ እንኳን ይህንን ውጤት ተሸናፊ ፖለቲከኞች በጸጋ ይቀበሉታል ማለት አይደለም:: ስለሆነም ይህ አማራጭ ከምንም አይነት ጥርጣሬ ውጪ የሆነና ፍጹም ተዓማኒነት ያለው ምርጫ ያካሂዳል ብሎ መገመት አስቸጋሪ ነው:: በተለይ በስልጣን ላይ ያለው ኃይል ይህን ምርጫ እስካሸነፈ ድረስ ጥርጣሬው በፍጹም የሚጠፋ አይሆንም::

ሁለተኛው አማራጭ በተለይ በምርጫ 97 ወቅት በምርጫው የተሳተፉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች በአማራጭነት ያቀረቡት አካሄድ ነበር:: በምክንያትነት የቀረበው በምርጫ ቦርዱ የሚሳተፉት ሁሉም የፖለቲካ ሀይሎች እስከሆኑ ድረስ ሂደቱ ለማንም የፖለቲካ ኃይል በማያደላ መልኩ እንዲካሄድ ያደርጋሉ፤ ውጤቱንም ለመቀበል ያስችላቸዋል የሚል መከራከሪያ ነበር:: ይህ መከራከሪያ መሰረት ያደረገው ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ነጻና ፍትሃዊ ምርጫን ይፈልጋሉ፤ ከዚህም ተጠቃሚ ናቸው የሚለው እሳቤ ነው:: ይህ ግን ሁሌም እውነት ነው ማለት አይቻልም:: ለውሳኔ በሚቀርብላቸው ጉዳዮች ላይ በቀረቡት ማስረጃዎች ፋይዳ ሁሉም ባይስማሙስ? በድምጽ ብልጫ ይወስኑ ካልን በድምጽ የተሸነፉት የፖለቲካ ሃይሎች ተወካዮች ያሸነፉትን ሁሉ “ምርጫውን አጭበረበሩ” ብለው ላለመክሰስ ምን ይከለክላቸዋል? ይህንንስ የሚያደርጉ ከሆነ (ምንም እንኳን ክሳቸው ውኃ የማይቋጥር ቢሆን) ደጋፊዎቻቸውንና በምርጫው ውጤት ያልተደሰተውን ሁሉ በምርጫው ተዓማኒነት ላይ ጥርጣሬ እንዲኖር ስለዚህም ስሜት በማነሳሳት ወደ ግጭት እንዲሄድ አያደርጉም ወይ? ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የለም:: የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሃይሎች ስብጥር በደንብ ለሚያውቅ ግን ይህ አይሆንም ብሎ ሊምል አይችልም:: ይህ ሞዴል ግን ከዚህም ያለፈ ያሰራር ችግር ሊገጥመው ይችላል:: የተለያየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው በመሰረታዊ መንገድ የማይተማመኑ ኃይሎች ባንድ ላይ ሆነው በየጊዜው በሚያደርጉት መጓተት የምርጫ አስፈጻሚው አካል በእርግጥም የተቀላጠፈና ብቃት ያለው ሥራ መስራት ይችላል ወይ የሚለውን ጥያቄ በአወንታዊነት መመለስ አይቻልም:: ይልቁንም ኮሚሽኑ ራሱ የግጭት አመንጪ ሊሆን የሚችልበት እድሉ የሰፋ ነው::

በነኝህና ተመሳሳይ ምክንያቶች እነኝህ ሁለቱም የተለመዱ ሞዴሎች በተለይ አሁን ባገራችን የፖለቲካ ሃይሎች ዘንድ ያለውን አለመተማመን ሊያከስም የሚችል ተቀባይነት ያለው ወደ ተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚያሻግር ምርጫ ሊደረግ ይችላል የሚል እምነት የለኘም:: ስለዚህ ከነኝህ ከተለመዱ አካሄዶች ወጣ ያሉና ያልተለመዱ ደፋር አካሄዶችን መቃኘቱ ይጠቅማል:: ከዚህ አንጻር ሁለት አማራጮችን በጥንቃቄ መመልከቱ ይበጃል እነኝህም:

በሽግግሩ ወቅት በሥልጣን ላይ ያሉ ኃይሎች ወይንም በሽግግሩ መንግሥት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑት ኃይሎች በመጀመሪያው ምርጫ ላይ እንዳይሳተፉ ማድረግ
የመጀመሪያውን ምርጫ ምንም ኢትዮጵያዊ ኃይል ሳይኖርበት ምርጫ የማካሄድ ልምድ፤ ክህሎትና፤ ገለልተኛነት ያለው የውጭ ሀገር መንግሥት ወይንም መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም በሙሉ ሥልጣን እንዲያካሂደው መስማማት::
እነኝህን ሁለት ያልተለመዱ አማራጮች ከነ አወንታዊና አሉታዊ መከራከሪያቸው አቅርቤ በእኔ እምነት የተሻለውን በመምረጥ ይህንን ውይይት ላጠቃል::

የመጀመሪያው አማራጭ ጠንካራ ጎኖች ያሉትን ያክል ተግባራዊነቱን የሚያሰናክሉ ደካማ ጎኖች አሉት:: ከጠንካራ ጎኖቹ ውስጥ ምናልባት ዋናው በሽግግሩ ወቅት ስልጣን ላይ ያሉ ኃይሎች በመጀመሪያው ምርጫ ላይ ምንም ቀጥተኛ የሆነ የራስ ጥቅም ከሌላቸው (በምርጫው ስለማይሳተፉ) ምርጫውን ያለምንም ወገንተኛነት ለማካሄድ ይችላሉ የሚለው ነው:: በዚህ ሁኔታ የሽግግሩን ስልጣን የያዙ ሰዎችን ወይንም የፖለቲካ ቡድኖችን የሚገፋፋቸው ወይንም የሚያገኙት ጥቅም (incentive) የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲፈጠር የማየት ፍላጎት ነው ማለት ነው:: ይህ ከሆነ ደግሞ ምርጫውን ያለወገንተኛነት ከማካሄድም በላይ በሽግግሩ ወቅት መሰራት ያለባቸውን ከላይ የዘረዘርናቸውን ስራዎች በብቃትና በንጽህና የመስራት ፍላጎታቸው ከፍተኛ ይሆናል ብሎ መጠበቅ ይቻላል:: ሌላው የዚህ አማራጭ በጎ ጎን በሽግግሩ ሂደት ማን ይሳተፍ የሚለውና የብዙ መጓተት ምክንያት የሆነውን የውስጥ ፍላጎትና ግፊት፤ ስለዚህም በፖለቲካ ኃይሎች መሀከል ያለውን ጥርጣሬና አለመተማመን፤ ይቀንሰዋል የሚል ነው:: ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት በሽግግሩ ላይ መሳተፍ ለዘላቂው ስልጣን መወጣጫ ይሆናል ብለው የሚያስቡና የሚጓጉ ኃይሎች በሽግግር መንግሥቱ መሳተፍ እንዲያውም ከዘላቂው ሥልጣን የሚያቅብ መሆኑን ሲያውቁ በሽግግሩ ወቅት ባለ ስልጣን የመሳተፍ ፍላጎታቸውን ያቆሽበዋል[3]፤ ይህ ደግሞ የሽግግሩ ሥራ ንጹህ የመሆኑን እድል በዚያው ልክ ያሰፋዋል:: ከዚህ ጋር የተያያዘው ሌላው ጥቅም ደግሞ ከሽግግሩ በኋላ በምርጫ በስልጣን ላይ የሚወጣው መንግሥት የሽግግሩን ሥልጣን ከያዘው የተለየ እንደሚሆን ከወዲሁ ከታወቀ፤ የሽግግሩን ስልጣን የያዙት ኃይሎች ወደፊት ከሚመጣ ተጠያቂነት ራሳቸውን ነጻ ለማድረግ ጠንክረው ይሰራሉ፤ ስለዚህም ሽግግሩን ተአማኒ ብቻ ሳይሆን በሽግግሩ ወቅት የሚፈጠሩት ተቋማት በእርግጥም ከመጪው መንግሥት ስራ አስፈጻሚ ኃይል ነጻ ሆነው እንዲሰሩ የማድረግ እድላቸው የሰፋ ይሆናል የሚል ነው::

ባንጻሩ ይህ አካሄድ የራሱ የሆኑ ችግሮች አሉበት:: የመጀመሪያው የወያኔን መውደቅ እውን ያደረጉት ሃይሎችና የወደቀበት መንገድ ሳይታወቅ በጥቅሉ ይህን አማራጭ ለውጡን ያመጡት ሃይሎች በሙሉ ልብ ይቀበሉታል ለማለት አይቻልም:: ከዚያም በላይ ግን ወያኔን በመጣል ሂደት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ምስረታ ጠንካራ ፍላጎትና ራዕይ አለን ብለው የታገሉ ኃይሎችን ሥርዓቱን ለመፍጠር በሚደረግ ምርጫ መሳተፍ አትችሉም የሚል ስምምነት ማስቀመጥ የነሱን መብት መጋፋት ብቻ ሳይሆን ሃገሪቱንም ጠንካራና የዴሞክራሲ ወገንተኛ የሆኑ መሪዎች ሊያሳጣት ይችላል:: ህዝቡንም የሚፈልገውን እንዳይመርጥ ማእቀብ ያደርግበታል:: ከዚህ በተጨማሪ ግን በሽግግሩ ወቅት የመንግሥት ስልጣን የያዙ ኃይሎች እራሳቸው እንኳን በምርጫው ባይወዳደሩ ከሚወዳደሩት መሀከል በአንድ ምክንያት ወይንም በሌላ ለሚመርጡት ኃይል አያደሉም ብሎ አፍን ሞልቶ ለመናገር ይከብዳል:: የምርጫ ኮሚሽኑ ጠንካራና በእውነትም ነጻ እስካልሆነ ድረስ በጊዜው በስልጣን ላይ ያለው ኃይል ስለማይወዳደር ብቻ ምርጫው ተዓማኒ ይሆናል ማለት አይቻልም::[4] ስለዚህ ይህ አማራጭ ቀደም ብለው ከተቀመጡትና በተለምዶ ከሚሰራባቸው ሞዴሎች የተሻለ ተዓማኒ የመሆን እድል ያለው ቢሆንም በውስጡ ያዘላቸው ድክመቶች በቀላሉ የሚታለፉ አይደሉም:: ተግባራዊነቱም ለውጡን ባመጡት ኃይሎች መልካም ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሰረተ ይሆናል::

የመጨረሻውና በእኔ እይታ ከሁሉም የተሻለ አማራጭ ነው ብዬ የማምነው የመጀመሪያውን ምናልባትም ሁለተኛውን ጨምሮ (ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እስከሚደረግ ድረስ) ምርጫውን ከሁሉም በሃገሪቱ ካሉ የፖለቲካ ኃይሎች ፍጹም ገለልተኛ በሆነ ሶስተኛ ሀገር ወይንም የሶስተኛ ሀገር ነጻ ተቋም እንዲደረግ ማድረግ ነው:: ይህ ሶስተኛ ሀገር በተቻለ መጠን እንደሀገር የተለየ ጥቅም (ጂኦ ፖለቲካዊ) ያለው መሆን የለበትም:: በገለልተኛነቱና በለዘብተኛነቱ የታወቀ፤ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓትና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ወገንተኛ መሆኑ ባለማቀፍ ደረጃ ብቻ ሳይሆን እስካሁን ከኢትዮጵያ ጋር ባለው ግንኙነት ያስመሰከረ፤ በሀገሪቱ ያሉትን የፖለቲካ ኃይሎች የማይጎረብጥ ሀገር መሆን ይኖርበታል[5]:: ይህ አማራጭ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በጥሩ ምሶሶ ላይ ለማቆም ብዙ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ምናልባት ሊያከራክር የሚችሉ አንድ ሁለት ድክመቶች ይኖሩታል:: ከድክመቶቹ እንጀምር:: እንዲህ አይነቱን አማራጭ የሚቃወሙ ሰዎች ሊያነሱ የሚችሉት አንድ መከራከሪያ እንዲህ አይነቱን ወሳኝ ሀገራዊ ስራ ለውጭ ኃይሎች መስጠት የሀገሪቱን ሉአላዊነት የሚነካ ምናልባትም የሀገሪቱን ክብር የሚያጎድፍ ሊሆን ይችላል የሚል መከራከሪያ ነው:: ይህ ግን በእርግጥም ክብረ ነክ ነው ቢባል እንኳን (እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ባለመፈጠሩ በሀገሪቱ ላይ የደረሰውና እየደረሰ ያለው ውርደት ከዚህ በጣም የከፋ ነው) ከሚሰጠው ጥቅም ጋር አብሮ ቢመዘን ያን ያክል ጠንካራ መከራከሪያ ነው ለማለት ያስቸግራል:: ሌላውና ምናልባትም የበለጠ ሊታሰብበት የሚገባው (ከዚህ በፊትም እኛ እስከምናውቀው ድረስ በተግባር ታይቶ ስለማይታወቅ) እንዲህ አይነቱን ሀላፊነት ለመውሰድ የሚፈልግ ገለልተኛ ሀገር ወይንም ተቋም ይኖራል ወይ? ከተገኘስ ወጪውን ማን ይችለዋል? የሚለው ነው:: ይህ ግን በሀገሪቱ ያሉት ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች (በሽግግር መንግሥት ስልጣን ላይ ያለው ኃይል ተጨምሮ) እስከተስማሙበት ድረስ እንዲህ አይነት የዴሞክራሲ ወገንተኛ መንግሥት ማግኘትና ይህም መንግሥት ወጪውን በእርዳታ መልክ ለመሸፈን ያስቸግረዋል ለማለት አይቻልም:: ይህን ውይይት ከዳር ለማድረስ ግን እንዲህ አይነት አካል ይገኛል በሚል እሳቤ የአማራጩን ጠንካራ ጎኖች እንመልከት::

በመጀመሪያ ብዙም ጥያቄ ውስጥ የማይገባው የእንዲህ አይነት ሃይል ገለልተኛነት ነው:: በሃገሪቱ ካሉት ኃይሎች ውስጥ አንዱ ወይንም ሌላው ቢያሸንፍ የሚያገኘው የተለየ ጥቅም ወይንም ጉዳት አይኖርም:: ይልቁንም የሃገሩ ወይንም የተቋሙ ታዋቂነትና ክህሎት (reputation) የሚመዘነው ምርጫውን በብቃትና በፍጹም ገለልተኛነት ማድረጉ ላይ ስለሆነ ለዚህ ጉዳይ አጽንኦት ሰጥቶ ይሰራል ተብሎ ይታሰባል:: ይህን ሃላፊነት የወሰደው ሃገር ይህ ስራ በብቃት መሰራቱን ማረጋገጥ ስላለበት (በምሳሌነትም በሌሎች ሃገሮች በአትኩሮት ስለሚታይ) በስራው ሰፊ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች ለስራው ያሰማራል ተብሎ ይጠበቃል:: በዚህ ሂደት ላይ እንዲህ አይነቱ ኃይል ወደፊት የሚካሄዱትን ምርጫዎች የሚመራውን ቋሚ የምርጫ ተቋም የመገንባትም ሃላፊነት አብሮ ከወሰደ ለወደፊቱም ጠንካራና ነጻ ተቋም የመገንባቱን ስራ በጣም ያግዘዋል:: በእንዲህ አይነት ፍጹም ገለልተኛ ሃይል የተካሄደ ምርጫ ተአማኒነት በሃገር ውስጥም ሆነ ባለማቀፍ ደረጃ ጠንካራ ነው የሚሆነው:: እንዲህ አይነት ጠንካራና ተዓማኒ ኃይል ይህን አስቸጋሪ ሥራ ከሽግግር መንግስቱ ጫንቃ ላይ ካነሳለት የሽግግር መንግስቱ ከላይ የጠቀስናቸውን እጅግ አስፈላጊና አድካሚ ስራዎች ላይ ሙሉ ኃይሉን ስለሚያሳርፍ እነኝህን የሽግግር ጊዜ ስራዎች በተሻለ ብቃት የመወጣት እድሉም ከፍተኛ ይሆናል:: የሽግግር መንግሥቱም ለዘላቂ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት ያለውን ቁርጠኛነት በዚህ ፍላጎቱ ብቻ በሀገሪቱ ላሉት የፖለቲካ ኃይሎችም ሆነ ለመላው ማህበረሰብ ግልጽ ያደርጋል:: ይህ ደግሞ በማህበረሰቡ ስነልቦና ላይ የሚኖረው አወንታዊ እንድምታ በቀላሉ የሚታይ አይደለም::

የዚህ አማራጭ ጥቅም ግን ከዚህም በላይ አሁን እየተካሄደ ያለውንም የዴሞክራሲ ትግል በማገዝ ላይም ነው:: ይህንን ውይይት ስጀምር በተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች መሀከል ይህንን ሥርዓት ለማስወገድ ፍላጎት እያለም ለምን መተባበር አልተቻለም? የሚለውን ጥያቄ በጥቅሉ የመለስኩት በተለይ ሽግግሩን በሚመለከት ባለው የመተማመን እጦት እንደሆነ ጠቁሜ ነበር:: ይህንን አማራጭ በሃገሪቱ ያሉ የፖለቲካ ኃይሎች ቢወያዩበትና ቢቀበሉት፤ በውስጣቸው ያለውን ከፍተኛ የጥርጣሬ ዳመና ምን ያክል ሊገፈው እንደሚችል ለመገመት አያስቸግርም:: ከዚህም በላይ ግን የፖለቲካ ሥልጣን በህዝብ ፍላጎትና ውክልና ሳይሆን ባቋራጭ በሚደረግ መደራደር ይገኛል ብለው የሚያምኑ የፖለቲካ ደካሞችን ከመድረኩ በማጥራት በኩልም ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል የሚል እምነት አለኝ:: በተለይም ደግሞ ወያኔ በጉልበት እንጂ በፍላጎቱ ስልጣን አይለቅም ብለው ነፍጥ አንስተው የሚታገሉ ኃይሎች እንዲህ አይነቱን አማራጭ በግልጽ ቢቀበሉት በትግሉ ሂደት እነሱ ስልጣን ከያዙ አይለቁም በሚል ፍርሃት በጥርጣሬ የሚያዩዋቸውንና በዚህም ምክንያት ትግላቸውን ከመደገፍ የሚታቀቡ ኃይሎችን ትግሉን እንዲደግፉ ማበረታታት ይችላል:: በሀገር ውስጥ በሚደረግ እንቅስቃሴ ከወያኔ ጋር በሚደረግ የምርጫ ሂደት ወያኔን ማባረር እንደማይቻል እያወቁም በሂደቱ የሚሳተፉ ሀይሎችም ከወያኔ የውሸት ምርጫ የተለየ ሰላማዊ አማራጭ በማቅረብ ማህበረሰቡን ለትግል ለማሰባሰብ፤ በወያኔ ላይም ከፍተኛ የሞራል ድል እንዲያገኙ ይረዳቸዋል:: ከሁሉም በላይ ግን ሰላማዊም ሆነ የአመጽ ትግል ለማድረግ የሚያስችል ከፍተኛ የሆነ የህዝብ የትግል መንፈስ ለማዳበር ይጠቅማል::

ማጠቃለያ: ወያኔን ለመጣል ጉልበት ያስፈልጋል የሚሉ ኃይሎች ይህን ሀሳብ ለምን እንዲደግፉት ይጠበቃል?

በዛሬ ጊዜ የሚደረግ፤ ከጉልበት ጋር የተያያዘ ትግል እንደቀድሞው የሚምል የሚገዘትበትና ለትክክለኛነቱ ምንም ጥርጣሬ የሌለው የኢኮኖሚ ወይንም ማህበራዊ ርዕዮተ አለም ይዞ የሚደረግ ትግል አይደለም:: ነፍጥ ያነሱ ኃይሎች ወደዚያ የተገፉት ሌላ አማራጭ በማጣት ነው:: ሁሉም የሚስማሙበት አንድ ዋና አላማ ቢኖር (ቢያንስ በፕሮግራማቸው ላይ ያስቀመጡት) ከምንም ነገር በላይ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ተመስርቶ ማየትን ነው:: ከዚህ አላማ ጋር የተያያዘውና የዚህ ትግል ስኬት አንዱ ወሳኝ ጉዳይ በማህበረሰባችን ዘንድ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደትን በሚመለከት የጠራ አመለካከት እንዲያዝ፤ በትግሉ ሂደት ደግሞ በሚፈጠረው ሥርዓት ዙሪያ ሰፋ ያለ ማህበራዊ መሰባሰብንና ፍላጎትን መፍጠር ነው:: ይህን ለማድርግ ለእንዲህ አይነቱ ሰፊ ማህበራዊ መሰባሰብ እንቅፋት ይሆናሉ ተብሎ የሚታሰቡ እክሎች እየተጠኑ የመፍትሄ ሃሳብ ማቅረብ፤ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎችን በነዚህ መፍትሄዎች ዙሪያ ማወያየትና ይህን አመለካከት እንዲጋሩ በዚህም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ማድረግ የታሰበው ውጤት ላይ ለመድረስ እጅግ አስፈላጊ ነው:: በዚህ የውይይት ሃሳብ ላይ የቀረበውን የመፍትሄ ሃሳብ በፖለቲካ ኃይሎችና በምሁራን ዘንድ መሸጥ ከተቻለ ትግሉን በማሳጠርም ሆነ በሚፈጠረው ሥርዓት ላይ የጠራ አመለካከት እንዲሁም ሰፋ ያለ የማህበረሰብ ድጋፍ (constituency for democracy) በመፍጠር ብሎም ሥርዓቱን እውን ለማድረግ የተጀመረውን ጉዞ ያሳካል የሚል እምነት አለኝ::

[1] ለዚህ ታሪካዊ ማስረጃ ካስፈለገ በአሁኑ ጊዜ በኢሕአዴግ ተቀርጾ የጸደቀውን ሕገ መንግስት በብዙ መልኩ የሚመስለውን በሶቭየት ሕብረት በእስታሊን አጋፋሪነት የጸደቀውን የ1936 ሕገ መንግሥት መመልከት ብቻ ይበቃል:: ይህ ሕገ መንግስት ብንመለከት በአንቀጽ 125 ላይ ያለምንም ሳንሱር የመጻፍ፤ የመናገር፤ የመሰብሰብ፤ የመደራጀት፤ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቶችን ያለምንም ገደብ ይፈቅዳል:: በአንቀጽ 134 ደግሞ ለሁሉም ላቅመ አዳም ለደረሰ ዜጋ በሚስጥር ድምጽ አሰጣጥ መሪዎቹን የመምረጥ መብት አልፎም በአንቀጽ 17 ደግሞ ማንኛውም የፌደሬሽኑ አካል የሆነ ክልል እራሱን የማስተዳደርና በሕዝብ ውሳኔ እስከመገንጠልና የራስን ሀገር እስከማቋቋም የደረሰ መብት ይሰጣል:: በተግባር የሆነውን ግን ሁላችንም የምናውቀው ነው::

[2] እንደሚታወቀው አንድ ሰው የመረጠውን አካባቢ ህዝብ ጥቅም የሚያስጠብቅ፤ ጥሩ ሕግ አውጪ ሊሆን ይችላል:: ይህ ማለት ግን ጥሩ ሀገራዊ መሪ ይሆናል ማለት አይደለም::

[3] ቆሸበ ማለት በእንግሊዘኛው supress the appetite የሚለውን ትርጉም የያዘ ነው::

[4] ባለፈው አመት በአፍጋኒስታን የታየው የምርጫ ቀውስ የቀድሞው ፕሬዜዳንት ካርዛይ በምርጫው ባይወዳደሩም እሳቸው የሚፈልጉትን ሰው ለማስመረጥ የምርጫ ኮሚሽኑን በመጠምዘዝ ኮሮጆ አስገልብጠዋል በሚል ነው:: በዚህም ምክንያት የምርጫ ኮሚሽኑ ሃላፊ ከስልጣናቸው ተነስተዋል::

[5] ከዚህ አንጻር የእስካንዲኔቪያ ሃገሮች ተመራጭ ይሆናሉ ብዬ አምናለሁ::

 

ሊቀመንበራችን ትግል ሜዳ ውስጥ ነው!- መግለጫ

$
0
0

def-thumb(መግለጫ, pdf)

ሐምሌ 12 2007 ዓ.ም.

ህወሓት በኢትዮጵያዊያን እና በኢትዮጵያ ላይ ያሰፈነው ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ እንዲያበቃ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈኑበት የፓለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት እንዲመሠረት እና የሀገራችን አንድነት በጠንካራ መሠረት ላይ ለማኖር አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ተገዶ የገባበት የመረረ የአመጽ ትግል መጀመሩን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ኢትዮጵያዊያን የነፃነት አርበኞች በጀግነትና በጽናት እየታገሉ ነው።

ይህ ትግል በባርነትና በነፃነት መካከል የሚደረግ ወሳኝ ትግል ነው። የዚህ ትግል ውጤት የእኛ የዚህ ዘመን ትውልድ ሕይወት ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የወደፊት ታሪክ፤ የልጅ ልጆቻችንን ሕይወት ይወስናል። በዚህም ምክንያት ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው። በዚህ ወሳኝ ወቅት ለነፃነት ግድ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከጎናችን ሊቆም ይገባል።

አርበኞች ግንቦት 7 አመራሩን ሁኔታዎች በፈቀዱ መጠን እና ትግሉ በሚጠይቀው ቦታ እንዲገኙ የሚያደርግ መሆኑ ሲገልጽ ቆይቷል። አሁን ትግሉ በደረሰበት ደረጃ የአመራሩ በትግሉ ሜዳ ውስጥ መገኘት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ሊቀመንበሩን ጨምሮ አመራሩን ወደ ትግሉ ሜዳ አንቀሳቅሷል። በዚህም መሠረት የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግል ሜዳ ወርዷል።

ትግሉ መሯል። ወሳኝ የሆነ ትግል ውስጥ ገብተናል። የትግሉ መሪዎች የሕይወት መስዋዕትነት እሚከፈልበት ቦታ ይገኛሉ። በአሁኑ ሰዓት የንቅናቄው አመራር በተሟላ ሁኔታ በትግሉ ሜዳ ውስጥ እንዲገኝ ማድረግ ተችሏል። ኢትዮጵያዊያን እጅ ለእጅ ተያይዘን ዘረኛው የህወሓት አገዛዝን ከጫንቃችን ለማስወገድ ቆርጠን እንድንነሳ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

ኢትዮጵያን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ የሚያወጣው አርበኞች ግንቦት 7 ብቻ አይደለም። ስለሆነም ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚደረገው ትብብር ቀዳሚ ትኩረት ከተሰጣቸው ሥራዎች አንዱ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ለድል እንዲበቃ ይታገላል። ኢትዮጵያዊያንም በያሉበትም በተመሳሳይ ልዩነቶቻቸውን አቻችለው በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ላይ ክንዳቸውን እንዲያነሱ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

እነሆ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በአካል ትግል ሜዳ ውስጥ ይገኛል። የሚችል ሁሉ እንዲከተል፤ መከተል የማይችል በያለበት ሁኖ ሁለገብ ትግሉን እንዲያጧጥፍ አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

ህወሓት በፈጠራቸው ድርጅቶች ውስጥ ተኩኖ ህወሓትን ማዳከም አርበኝነት ነው!

$
0
0

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ለኢህአዴግ እና አጋር ድርጅቶቹ አባላት የሚከተለው መልዕክት ማስተላለፍ  ይሻል።

def-thumbህወሓት ጥቂት አባላትና ደጋፊዎች ይዞ ታላቂቷን ኢትዮጵያ ለማንበርከክ እና ሀብቷን ለመመዝበር  እናንተን መጠቀሚያ ያደረጋችሁ መሆኑን የምታውቁት ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ የተባሉ ድርጅቶች የራሳቸው ድርጅታዊ ነፃነት የሌላቸው የህወሓት አገልጋዮች መሆናቸው እነሱ ራሳቸው የሚነግሯችሁ ከመሆኑም በላይ እናንተም በዕለት ተዕለት ተግባራችሁ የምትታዘቡት ሀቅ ነው። እነዚህ ድርጅቶች ህወሓትን ለማስደሰት ሲሉ የራሳቸውን ሕዝብ የሚያስሩ፣ የሚገድሉ፣ የሚዘርፉ፣ ከቀየው የሚያፈናቅሉ፣ መኖሪያ ቤቱን የሚያስፈርሱ መሆናቸው እናንተም እየተሳተፋችሁበት ያለ ሥራ ነውና የምታውቁት ነው። “አጋር ድርጅቶች” የሚል ስያሜ የተሰጣችው  አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊ እና ኢሶዴፓ “አጋር” ሳይሆን የህወሓት ጀሌዎች መሆናቸው እናንተም እኛም የምናውቀው ነው። እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ፣ አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ  የተባሉ አድርባይ ድርጅቶች ባይኖሩ ኖሮ ህወሓት ለ24 ዓመታት ኢትዮጵያዊያን እየገደለና እያሰረ፤ እየዘረፈ በውሸት ምርጫና በውሸት ዲሞክራሲ ስም ፍጹም የሆነ ዘረኛ፣ ከፋፋይ፣ አምባገነናዊ ሥርዓት በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያሰፍን ባልቻለም ነበር። ህወሓት በኢትዮጵያዊያን አናት ላይ እንዲፈነጭ እናንተ አባል የሆናችሁባቸው ድርጅቶች አስተዋጽዖ  ከፍተኛ  ነው።

ይህ ብቻም አይደለም። እናንተ አባል ሆናችሁ ድጋፍ ባታደርጉላቸው ኖሮ እነዚህ አድርባይ ድርጅቶች ባልኖሩም ነው። ስለሆነም ህወሓት በኢትዮጵያዊያን አናት ላይ እንዲፈነጭ፣ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ ልጆቻችሁ እና የልጅ ልጆቻችሁ በሎሌነት እንዲያድጉ፤ ጥቂቶች በልጽገው ብዙሃኑ እንዲደኸዩ  እናንተ በግል አስተዋጽዖ አድርጋችኋል።

ብዙዎቻችሁ እነዚህ አድርባይ ድርጅቶችን የተቀላቀላችሁት በኑሮ ግዴታ፣ በትዕዛዝ፣ በአማራጭ እጦት ሰበብ፣ የሰብዓዊ ተፈጥሮችን አካል በሆነው የመንፈስ ደካማነት ምክንያት እንደሆነ፤ ድርጅታችሁ በሕዝብ ላይ የሚያደርሰው በደል እያያችሁ ህሊናችሁ እንደሚቆስል እናውቃለን። አንዳንዶቻችሁ ውስጣችሁ እያነባ እጆቻችሁ ኢፍትሀዊ ተግባር እንደሚፈጽሙ እናያለን። ኢህአዴግ እንደማፊያ ድርጅት መግባት እንጂ መውጣት የማይቻልበት ሆኖ እንዳገኛችሁት እናውቃለን። “ይህንን ድርጅት ከለቀቅኩ የሚጠብቀኝ እስር፣ አልያም ሥራ ማጣት ነው። ያኔ ምን ይውጠኛል? ትዳሬ፣ ልጆቼ፣ ወላጆቼ እንዴት ይሆናሉ?” የሚል ስጋት እንዳለባችሁ እንገነዘባለን። ህወሓትን በመርዳት ያቆማችሁት ሥርዓት እንኩዋንስ ለሌላው ለእናንተም ከፍርሃት ነፃ ሊያደርጋችሁ አለመቻሉን እናውቃለን። ድርጅታችን አርበኞች ግንቦት 7፣ እናንተ ያላችሁበት አጣብቂኝ ቀላል እንዳልሆነ ይገነዘባል። በዚህም ምክንያት ይህንን ጥሪ ለእናንተ ያቀርባል።

ሀገራዊና ሕዝባዊ ስሜት ያላችሁ፤ ለራሳችሁና ለቤተሰቦቻችሁ ክብር የምትጨነቁ፣ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ ሎሌነትን  ሳይሆን ክብርን  ማውረስ የምትፈልጉ የኢህአዴግ እና የአጋር ድርጅቶቹ አባላት ሆይ! አባል የሆናችሁባቸውን ድርጅቶች ሳትለቁ፤ ኢህአዴግም ሆነ አጋር ድርጅቶቹ ውስጥ እያላችሁ ለህሊናችሁ፣ ለልጆቻችሁ፣ ለቤተሰቦቻችሁና ለሀገራችሁ የምትሠሩበት መንገድ ተመቻችቶላችኋልና ተጠቀሙበት።

የአገራችን የነፃነት ተጋድሎ ታሪክ እንደሚያስተምረን አርበኝነት ሁለት ዓይነት ነው። አንዱ በገሀድ፣ በግላጭ፣ በውጊያ ሜዳ የሚታይ አርበኝነት ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ፣ በጠላት ጉያ ውስጥ ተኩኖ፣ ጠላትን መስሎ  የሚደረግ አርበኝነት ነው። ሁለተኛው ዓይነት አርበኝነት በተለምዶ  “የውስጥ አርበኝነት” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በተግባርና በውጤት ከአደባባይ አርበኝነት በምንም የማይተናነስ የጀግንነት ሥራ ነው። የውስጥ አርበኛ፣ አርበኛ ነው። የውስጥ አርበኛ ገድሉ  በታሪክ የሚወደስ፣ በአርዓያነቱ የሚጠቀስ የሀገሩ የቁርጥ ቀን ልጅ  ነው።

የኢህአዴግ አባላት ሆይ የውስጥ አርበኛ የመሆን እድላችሁን አታስመልጡ!

ዛሬ በምንገኝበት ሁኔታ የውስጥ አርበኝነት ማለት ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደህዴድ፣ አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊ ወይም ኢሶዴፓ  ውስጥ ሆኖ ህወሓትን ማዳከም ማለት ነው። በእነዚህ ድርጅቶች ውስጥ ቀንደኛ የህወሓት ጉዳይ አስፈፃሚዎች እንዳሉ ይታወቃል። የውስጥ አርበኞች ተግባር እነዚህ ከህወሓት በላይ ህወሓት ሆነው እናንተ በወገናችሁ ላይ በደል እንትድፈጽሙ የሚያደርጓችሁ፤ ለህወሓት ባርነት መገዛትን መታደል እንደሆነ አድርገው የሚሰብኩ ቀንደኛ ባንዳዎችን መቆጣጠር ነው። የውስጥ አርበኛ ማለት በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ ሥርዓቱ የሚያዳክሙ ተግባራትን የሚሠራ ጀግና ማለት ነው። የውስጥ አርበኛ ማለት በሕዝብ ላይ በደል የሚሠራን ሥርዓት በአሻጥር የሚያሽመደምድ ብልህ ዜጋ ማለት ነው። የውስጥ አርበኛ ማለት አለቆቹን እየሰለለ፣ ራሱ የተሳተፈበትም ቢሆን የሥርዓቱን እቅዶች ለታጋዮች አሳልፎ የሚሰጥ ባለውለታ ማለት ነው። የኢህአዴግና “የአጋር” ድርጅቶች አባላት በውስጥ አርበኝነት በመሳተፍ ለህሊናችሁ፣ ለልጆቻችሁና ለልጅ ልጆቻችሁ ውለታ መሥራት ትችላላችሁ።

 

የህወሓትን ዓላማ የማይደግፉ የህወሓት አባላት እንዳሉም እናውቃለን። ለእነሱም ህወሓት ውስጥ ሆኖ ህወሓትን ማዳከም ትልቅ የውስጥ አርበኝነት እንደሆነ ማስገንዘብ እንወዳለን። የፍትህ፣ የእኩልነት፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ጉዳይ ከዘር በላይ መሆኑ የሚረዱ፤ እነሱ ለራሳቸው እንዲሆን የሚፈልጉት ሌሎች ኢትዮጵያዊያንም የሚመኙት መሆኑን የተረዱ የህወሓት አባላት የኢፍትሃዊነት ምንጭ የሆነው ድርጅታቸውን በማዳከም ላይ የመልካም ዜግነት አክሊል መቀዳጀት ይችላሉ።

በህወሓትና ህወሓት የፈጠራቸው ድርጅቶች ውስጥ የምትገኙ ወገኖቻችን ፈልጋችሁ አግኙን፤ ደህንነታችሁ በተጠበቀ  መጠን በዘረኛ ድርጅት ውስጥ ሆናችሁ ዘረኝነትን፤ በፋሽስት ድርጅት ውስጥ ሆናችሁ ፋሺዝምን መዋጋትና ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ መኖር ትችላላችሁ። ይህን ስትሰሩ እኛ ከናንተ ጋር ነን። ይህንን ስትሠሩ እኛና እናንተ ለጋራ ዓላማ የምንሰራ ጓዶች  እንጂ ጠላቶች አንሆንም። ሥርዓቱን በማዳከም ረገድ የምትወስዱት ተጨባጭ እርምጃዎችን ማየት እንፈልጋለን። እኛን ማግኘት ከባድ አይደለም፤ ፈልጋችሁ አግኙን። ተባብረን አገራችን ከህወሓት  ፋሽስታዊ ዘረኛ አገዛዝ ነፃ  እናውጣ።

 

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Q&A: Professor Berhanu Nega – Bucknell University

$
0
0

dr-berhanu-NegaIn December, an Ethiopian court sentenced Professor of Economics Berhanu Nega to death in absentia for terrorism.

Q: Your colleagues and friends understand that this charge is bogus, but do you hear from others who don’t?

A: I haven’t heard from any one who takes this as a serious judicial decision. Only the Ethiopian government and its blind supporters take this decision seriously. Even the government knows that the decision of the court is nothing but a reflection of the regime’s desires rather than based on any reasonable evidence. It sends a message to the public — there is no court to save you, you live by our rules, if you question our rules, we will do what we want, and no one will stop us.

Q: The death sentence is real, and you were jailed under the Zenawi government. Are you afraid?

A. One of the reasons that you struggle for freedom and liberty is because you feel that life isn’t meaningful without liberty. I don’t want to think about this in a way that would affect my day-to-day existence. I am not worried not because the government would not try to harm me, but I now live in a society of laws that will protect me. You can’t live in fear. If you allow this kind of fear to determine your actions, dictatorships will exist forever.

Q: What sustained you when you were imprisoned?

A: First, the Ethiopian people and their yearning for freedom. While I was incredibly disappointed by U.S. and European policy makers and diplomats at the time, while I was in prison, I also was hearing about Bucknell, my colleagues, students and people at other universities supporting freedom. People who love liberty and stand by your side — that’s the more endearing attachment. This connection at the human level, that people love and support freedom everywhere, recognizing that freedom is a human condition, is the hope for humanity that keeps you going. It was a source of hope for me when I was in prison, and I suspect for all people fighting for liberty around the world.

Q: What is your hope for Ethiopia?

A. Unless the international community takes the position of outrage as it did in Guinea, the government will not change. The brutality of this regime is mind boggling. This is a government that is known for committing genocide against its people. This is a most hated government because it is not only undemocratic, it is ethnocentric. Its basic strategy is to stay in power by terrorizing people and by dividing them on primordial grounds. There are several groups fighting against the government. Unless there is a serious intervention, the whole region will blow up. I encourage Western policymakers to recognize what is happening and adjust their policy before it is too late to make a difference. The only credible and durable solution for the region, in my view, is the democratization of Ethiopia.

Source: http://www.bucknell.edu/

Letter to President Obama ahead of visit to Kenya and Ethiopia (Human Rights Watch)

$
0
0

President Barack Obama
The White House
1600 Pennsylvania Avenue NW
Washington, DC 20500

Re: Your visit to Kenya and Ethiopia

Dear Mr. President:

As you prepare to visit Kenya and Ethiopia later this month, we, the undersigned organizations and individuals, write to share our appreciation for your engagement on some key concerns on the sub-continent, including the crucial role of governance. To this end, last summer’s US-Africa Leaders Summit was an important milestone and your upcoming trip presents an opportunity to reaffirm your administration’s commitment to addressing the core challenges faced by millions of Africans.human-rights-watch

As key partners for the United States, both Kenya and Ethiopia present pressing human rights concerns that we hope will be at the forefront of your discussions. While both countries face real security threats, we are concerned by the way in which each government has responded, often with abusive security measures and increased efforts to stifle civil society and the media. Many of these initiatives undermine core human rights protections and the rule of law and are also counterproductive when it comes to reducing insecurity. We urge you to clearly articulate that the United States expects its partners to support an environment where independent organizations and media outlets can thrive, and security forces undertake operations that protect – rather than abuse – their citizens.

Kenya

Your long-awaited trip to Kenya offers key opportunities to address both new and longstanding challenges with which the country continues to grapple – from security force impunity and the need for criminal justice reforms, to an increasingly restrictive environment for media and civil society, and growing pressure on Kenya’s Somali refugee population and its Muslim communities.

Accountability for Abuses by the Security Forces. As you are aware, the Kenyan police and other security forces have long committed serious human rights violations with impunity. This lack of accountability was identified as a crucial area for reform in the wake of the 2007-2008 post-election violence and remains a central challenge. More recently, credible research by a number of independent organizations has implicated the Anti-Terrorism Police Unit (ATPU), along with other security forces, in serious abuses in Nairobi, on the coast and in the northeast. They have routinely responded to alleged attacks by the armed group Al-Shabab with abusive operations that appear to target specific communities – Muslims, Somali Kenyans and Somali refugees – based on their ethnicity, nationality or religion. Such actions risk further undermining confidence in the security forces, rendering them less effective, and fueling radicalization instead of countering it.

We hope you will use your visit to Kenya to press President Uhuru Kenyatta and his administration to take the necessary steps to reverse these trends. In particular, this includes the need to investigate reports of security force abuse and prosecute those responsible for serious crimes, while ensuring that independent oversight mechanisms such as the Independent Policing Oversight Authority are adequately resourced and able to effectively perform their work free from interference.

Meaningful efforts to address broader questions of impunity also entail cooperating with the International Criminal Court (ICC) and revisiting domestic efforts to investigate and prosecute serious crimes committed during the 2007-2008 post-election violence. The communal grievances that underlay that violence remain and will continue to fester if left unaddressed. In general we urge you to stress that abusive operations against Muslim and ethnic Somali communities are not only unlawful but also an ineffective response to security threats. It is critical for the national security interests of both the US and Kenya that Kenyan security force actions do not reinforce Al Shabab’s one-sided public narratives.

Restrictions on civil society. Kenya’s nongovernmental organizations have enjoyed a relatively open environment consistent with the rights to freedom of association and expression for more than a decade, but over the past year that has begun to change. The Kenyan government has increased legislative efforts to restrict both nongovernmental and media work, and government officials have repeatedly voiced hostility and suspicion of independent voices. In recent months, Muslims for Human Rights (MUHURI) and Haki Africa, two human rights organizations working to document abuses in counterterrorism operations on the coast, have faced an onslaught of administrative harassment, including arbitrary searches and seizure of documents, freezing of bank accounts, suspension of insurance coverage, and de-registration, despite a court order establishing that they have no links to terrorist groups.

We appreciate the many efforts by your administration – and specifically by Ambassador Robert Godec – to support these two organizations and civil society in general. We urge you to continue sending an explicit message, both in public and in private, that the protection of civil society organizations – in line with your September 2014 Presidential Memorandum on Civil Society – is a top priority for your administration and that any new legislation should respect international standards on freedom of expression and association.

Refugees. For decades, Kenya has played a crucial role in the region by providing refuge to hundreds of thousands of Somali refugees. But unsubstantiated allegations that Somali refugees pose a security threat have increased in the wake of the Garissa University attack, as have statements that they should now all return to Somalia. To date, the authorities have produced no evidence that Somali refugees provided material support to armed militants. Over the past six years, many independent organizations have documented how refugee communities in Dadaab and Nairobi are routine targets for harassment, extortion, and mistreatment by police and other security forces. Your administration has been extremely vocal about the need for the Kenyan authorities to register and protect its refugee communities, including those from Somalia. We urge you to remind President Kenyatta of his recent pledges and obligations under both African regional and international refugee law to respect the principle of non-refoulement, ensure that refugees are protected and assisted, and consider durable long-term solutions for the refugee population.

Ethiopia

While part of your trip to Ethiopia will include a momentous visit to the African Union, we are concerned by the timing of your bilateral meetings with Ethiopia’s leadership. Particularly in the wake of that country’s recent non-competitive elections, your visit may send the message that the United States is giving short shrift to the profoundly repressive policies pursued by the government. The political environment in Ethiopia is dramatically restricted, as is the ability for Ethiopians to freely express themselves. Over the past decade, a range of measures has been adopted that sharply curtail fundamental liberties.

As you know, under Prime Minister Meles Zenawi, the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) government made economic gains and apparent improvements in socio-economic indicators. However, since the 2005 election crisis the ruling party’s political dominance, repression of political opposition parties, and restrictions on the media and civil society have increased dramatically.

Instead of providing leadership in the region on human rights, Ethiopia has regrettably become a model for draconian legislation that restricts freedom of speech and association. Its anti-terrorism law has been primarily used to target journalists and others critical of government policies. These laws are not only misused for political prosecutions in Ethiopia, they are increasingly a model for repressive legislation across the region. In addition, over the past 15 years, Ethiopia’s security forces have committed war crimes and possible crimes against humanity, most notably in the Somali region, without any credible investigations or prosecutions.

We urge you to make clear in all your meetings that the recent release of six journalists and bloggers is welcomed, but is only a preliminary step towards more meaningful and sustainable reforms. Scores of other journalists, political opposition leaders, and protesters who have been arbitrarily detained or wrongfully imprisoned for exercising their rights should urgently be released. The July 6 conviction of 18 Muslim journalists and activists is an especially worrying sign. Moreover, Ethiopia needs to amend the Charities and Societies Proclamation and the Anti-Terrorism Proclamation, both of which are core tools used to prosecute and restrict dissenting voices. These laws need to be revised to conform with international human rights standards on freedom of expression, association, peaceful assembly, and fair trial standards.

Finally, we urge you to raise the need to address impunity by Ethiopia’s security forces for a wide range of serious human rights violations, including routine torture of political detainees, extrajudicial executions and rape by military forces in various regions, and other serious crimes. The government should reverse its reflexive denials of abuse and restrictions on independent human rights investigations and reporting.

We believe it is essential for you to highlight, along with the positive change and growth that will underpin your visit, the many challenges discussed above. As you said in your Ghana speech in 2009, “history offers a clear verdict: governments that respect the will of their own people are more prosperous, more stable, and more successful than governments that do not.” We continue to believe in this message and the need for it to be reinforced on your upcoming trip.

Thank you for your time and consideration of these important issues.

Sincerely,

Bronwyn E. Bruton
Deputy Director, Africa Center
Atlantic Council

John Campbell
Senior Fellow
Council on Foreign Relations

Brian Dooley
Director, Human Rights Defenders
Human Rights First

John Harbeson
Professor Emeritus
CUNY Graduate Center and City College of New York

Steven Hawkins
Executive Director
Amnesty International USA

David Kramer
Senior Director for Human Rights and Democracy
The McCain Institute for International Leadership

Mark Lagon
President
Freedom House

Princeton Lyman
Senior Advisor to the President
United States Institute of Peace

Sarah Margon
Washington Director
Human Rights Watch

Sarah Pray
Senior Policy Analyst
Open Society Policy Center

Jeffrey Smith
Advocacy Officer
Robert F. Kennedy Human Rights

David Throup
George Washington University and Johns Hopkins SAIS

Mark Yarnell
Senior Advocate
Refugees International

Amb. (Ret) William M. Bellamy
Warburg Professor of International Relations
Simmons College

Source: https://www.hrw.org/

ህወሓት ለሽብር ጥቃት ተዘጋጅቷል፤ እንጠንቀቅ

$
0
0

def-thumbዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ፣ በሕዝባዊ ኃይሎች ላይ ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ተቀባይነት እንዲያገኝለት የሽብር ተግባር ፈጽሞ በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ ለማላከክ ወስኗል። እንዲህ ዓይነቱ እኩይ ተግባር ህወሓት ስልጣን ከመያዙ በፊትም በኋላም ሲያደርገው የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ህወሓት እንዲህ ዓይነቱ ኢሰብዓዊና ዘግናኝ ተግባር ለመፈፀም የሚያስችሉ እኩይ ስለልቦና እና ልምድ አለው።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በቅርቡ የጀመረው የነፃነት ትግል የፈጠረበት መደናገጥ ለመሸፈንና ንቅናቄውን በኢትዮጵያ ሕዝብና በዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብ ለማስወገዝ ያግዘኛል ብሎ ያመነበት ይህን ዘግናኝ ሴራ ከሳምንት በፊት ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁቱን አጠናቆ የነበረ ቢሆንም በወቅቱ የነፃ ሚዲያ አባላት ደርሰውበት ለሕዝብ ይፋ በማድረጋቸው እንዲዘገይ ተደርጎ ነበር። አሁን በደረሰን መረጃ ደግሞ ሴራው ከበፊቱ በባሰ እና ይበልጥ አውዳሚ በሆነ መጠን ተግባራዊ ለማድረግ የህወሓት “ስውር” መንግሥት ወስኗል። በዚህም ምክንያት ይህ የማስጠንቀቂያ መግለጫ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ በማያሻማ ሁኔታ እንዲገነዘብ የምንፈልገው ሀቅ የሚከተለው ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በደረሰው መረጃ መሠረት ህወሓት በሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ወስኗል። የእቅዱ ዓላማ ዘግናኝ እርምጃ በንፁሃን ዜጎችና ሕፃናት ላይ በማድረስ “የሽብር ጥቃቶች ሰለባ” ነኝ በማለት የኢትዮጵያ እና የዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ አዘኔታ ማግኘት ነው። የዩ. ኤስ. አሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን የሚጎበኙ መሆኑ ደግሞ ይህንን እቅድ ተግባራዊ የማድረግ ጉጉቱ እንዲጨምር አድርጓል። ስለሆነም ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ በህወሓት የሽብር አደጋ ውስጥ ነች። የቦሌ ዓለም ዓቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ እና ወደዚያ የሚያደርሰው መንገድ፣ የአፍሪቃ ኅብረት ጽ/ቤት እና የአሜሪካ ኤምባሲ ህወሓት በሽብር ጥቃት ዒላማነት ከመዘገባቸው ውስጥ ቀዳሚዎቹ ናቸው።

አርበኞች ግንቦት 7 በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚቃጡ የሽብር ጥቃቶችን መቃወም ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ተባብሮ ያመክናል። ይህ በህወሓት የተደገሰልንን የሽብር ጥቃት ማምከን ይኖርብናል። እኩይ እቅድን አስቀድሞ አውቆ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ አንድ ዓይነተኛ የሽብር መከላከያ ዘዴ ነው። በዚህ ረገድ በአገዛዙ ውስጥ ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ባለውለታዎች ናችሁ።

የእያንዳንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሕይወት መለኪያ በሌለው መጠን ውድና ክቡር ነው። በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ዜጋ የህወሓትን እኩይ ሴራ ተገንዝቦ ራሱን፣ ቤተሰቡንና አካባቢውን ከጥቃት እንዲጠብቅ አርበኞች ግንቦት 7 በጥብቅ ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!


TPLF Security Forces Terrorist Plot in Addis Ababa Leaked

$
0
0

def-thumbPatriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy has received credible reports that the fascist regime in Ethiopia has made intricate plans to detonate explosives and blame Patriotic Ginbot 7 for its own terrorist acts.

While we had received the leaked information of the sinister plans being hatched by the TPLF politburo members a few weeks ago, the pending visit of the U.S. President to Ethiopia have made it imperative for the TPLF regime to carry out the heinous crimes in the next few days.

We would like to inform the Ethiopian people and the international community that TPLF has finalized plans to carry on terrorist acts at Bole International Airport, along the major highway leading to the airport, at the headquarters of the African Union and the U.S. Embassy.

The TPLF minority regime is, of course, no stranger to planting bombs in Ethiopia’s capital Addis Ababa in a bid to frame its real and perceived political enemies and brutally murder innocent Ethiopians.

Massive leaks of secret files by WikiLeaks has exposed the late Prime Minister Meles Zenawi as the terrorist-in-chief. In a report from 2006 marked “Secret; Subject: Ethiopia: Recent Bombings Blamed on Oromos Possibly the Work of Government of Ethiopia” “Classified By: Charge [d’Affairs] Vicki Huddleston”, “An embassy source, as well as clandestine reporting, suggests that the bombing may have in fact been the work of the Government of Ethiopia security forces.” (Cable reference id:#06ADDISABABA2708.)

Patriotic Ginbot 7 strongly condemns the senseless brutality and the unconscionable use of terror by the rogue regime in Ethiopia to garner international support. Its utter disregard for the sanctity of human life and the Ethiopian people’s well known reputation as a peaceful and cultured people who abhor violence is truly horrifying.

The very fact that this dying regime is willing to kill, maim and cause mayhem in Addis Ababa to maintain power at any cost and in the face of a shrinking political base is a clear indication that it has lost any legitimacy to rule Ethiopia.

Patriotic Ginbot 7 would like to remind the deeply traumatized people of Ethiopia who are knowledgeable of the sinister motives of the fascist regime to be ever so vigilant and take every precaution for their individual and collective safety.

It is also time for the United States and the international community to realize that a terrorist regime willing to use violence to cling to power will never be a credible partner in the “war against terror.”

Friday, July 24, 2015

ሁሉም በያለበት የነፃነት ትግሉን ይቀላቀል!!!

$
0
0

def-thumbእኛ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የሰውነት መብታችን ተገፎ የዜግነት ነፃነታችን ተረግጦና ተዋርደን የምንገኝበት ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው፡፡ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ እስርና የጅምላ ስደት እንደ ዘመነ ወያኔ የታየበት ዘመን የለም፡፡ ህፃናት በረሀብ ከሚማሩበት ክፍል ውስጥ የሚወድቁበት ፤ ወንድ ልጅ በደህንነት ሀይሎች ታፍኖ የሚደፈርበት፤ ሴት ልጅ በገመድ የታሰረ የባልዋነወ ብልት መንገድ ለመንገድ እንድትጎትት የተደረገበት ዘመን ቢኖር ያሳለፍነው የወያኔ ዘመናት ብቻ ነው፡፡ ባጠቃላይ የሰው ልጅ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ መከራና ሰቆቃ እንድንሸከም የተገደድንበት ዘመን ላይ እንገኛለን፡

በአንፃሩም ስለ ለፃነት ስለ ፍትህና እኩልነት ሲሉ የተሰዉ ዋጋም የከፈሉ፤ አሁንም እየከፈሉ የሚገኙ ጥቂት አይደ ሉ ም፡፡ ከነዚህም አንዱ አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ይህ ለነፃነት ለፍትህና ለ ዲሞክራሲ የሚደረገው ተጋድሎ ውሎ አድሮ ዛሬ ከዋናውና ወሳኝ ከሆነው ምእራፍ ላይ መድረሱ ደግሞ የሁላችንንም ተስ ፋ ያለመለመና የተደፋው አንገታችን ቀና ያደረገ መሆኑና በተቃራኒው የወያኔን ካንፕ ያሸበረ መሆኑ በገሀድ እየታየ የሚገኝ እውነት ነው፡፡

እንግዲህ ይህን ወራዳ ስርአት አስወግዶ በምትኩ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመተካት የሚደረገው ትግል ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የተደረገው ርብርብ ቀላል ባይሆንም ቀሪውን አጠናቆ ከዳር ለመድረስ ከመቼውም ጊዜ በላይ የእያንዳዱን ኢትዮጵያዊ የተግባር ተሳትፎ የሚጠይቅ፤ ሁሉም ከያለበት ስለ ነፃነት የሚደረገውን የአርነኝነት ትግል በመቀላቀል የድርሻ ውን ሀላፊነት መወጣት ከሚጠይቅበት ወሳኝ ምእራፍ ላይ መድረሳችንን መረዳት ግድ ይላል፡፡

እኛ ኢትዮጵያውያን ያለ ማንም እርዳታና ድጋፍ ዋጋ ከፍሎ ለፃነትን የማሰከበር እንግዳ ሳንሆን በታሪክ የምንታወቅበት መለያችን መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ እንኳን ዛሬ አለም አለም በጠበበችበት ዘመን ቀርቶ ትናንት በጨለማው ዘመን እንኳ እነ ዶ/ር መላኩ በያን ከአኛ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት ፈር ቀዳጅ ሆነው የተገኙበትን ታሪክ ማስታወስ ይገባል፡፡

እናም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኟውም ስፍራ የሚገኝ ሁሉ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል እውቀት ያለው በእውቀቱ፤ ጉልበት  ያለው በጉልበቱ፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ለመደገፍ ዛሬ ነገ ሳይል አሁኑኑ ከአርበኝነቱ ትግል መቀላቀል ይጠበቅበታል፡፡ ኢትዮጵያዊነታችንን ብቻ ሳይሆን ሰው መሆናችን የሚረጋገጠው ነፃነታችንን አስጠብቀን በነፃነት መኖር ስንችል ብቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡

ስለዚህ ዛሬ አርበኞች ግንቦት ሰባት የለኮሰው የነፃነት ቀንዲል ከነጻነት አደባባይ ለመትከል የጀመረውን ጉዞ በሰው ሀይል፤ በገንዘብና በቁሳቁስ በማገዝ ሁላችንም የድርሻችንን እንድንወጣ ጥሪ ስናደርግ ለእኛ ኢትዮጵያውያን ከእኛ ኢትዮጵ ያውያን ውጭ ማንም እንደሌለ በማስገንዘብ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

በሙስሊም እንቅስቃሴ መሪዎች ላይ የተሰጠውን ፍርደገምድል ፍርድን እናወግዛለን!

$
0
0

def-thumbየህወሓት አገዛዝ የሚዘውረው የይስሙላ ፍርድ ቤት ዛሬ ሀምሌ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. በሙስሊም ወገኖቻችን መሪዎች ላይ ፍርደገምድል ውሳኔ ሰጥቷል። በዚህ ውሳኔ መሠረትም የእምነት መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው በሰላማዊ በሆነ መንገድ የጠየቁ ወገኖቻችን መሪዎች እስከ 22 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄዎቻቸው ሰላማዊ በሆነ መንገድ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ሥርዓቱ ያደረገውን ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን ተቋቁመው “ድምፃችን ይሰማ!” የሚል አቤቱታ ከማቅረብ የዘለለ አንዳችም የኃይል እርምጃ ወስደው አያውቁም። ሆኖም “በደል ደርሶብኛልና ልሰማ” ብሎ አቤቱታ ያቀረበ ሕዝብ መሪዎችን እስከ ሃያ ሁለት ዓመታት በእስር መቅጣት የአገዛዙ እብሪትና ማናለብኝነት አጉልቶ የሚያሳይ ተግባር ነው።

አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህን ፍርደገምድል ውሳኔ አጥብቆ ያወግዛል።ይህ ፍርደገምድል ውሳኔ የተሰጠው ፕሬዚዳንት ኦባማ በአገራችን መዲና ተገኝተው “ለሰላም ሲባል ነፃነትን ማፈን ሁለቱንም ያሳጣል” ባሉ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሆኑ አገዛዙ የሚሰማ ጆሮ የሌለው መሆኑ የሚያረጋግጥ ሆኗል።

የሙስሊም መሪዎች በእስር ላይ በነበሩት ጊዜ በምርመራ ስም ተደብድበዋል፤ ክብራቸው ተደፍሯል፤ የተለያዩ ዘግናኝ ሰቆቃዎች ተፈጽሞባቸዋል፤ የሀሰት ዶክመንታሪ ፊልሞች እንዲሰራጩ ተደርገው ስማቸውን ለማጥፋት ሙከራ ተደርጓል።

በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የደረሰው በደል ሃይማኖት ሳይለይ በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰ በደል ነው፤ መፍትሄ የምናገኘውም በጋራ በምናደርገው ትግል ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና የአገር አንድነት የሚጠብቅ የመንግሥት ሥርዓት ስናቆም ነው። ከዚህ በመለስ የሚገኝ መፍትሄ የለም። የእምነት መብቶች የሚከበሩት ሰብዓዊ መብቶች ሁሉ ሲከበሩ እንደሆኑ “በድምፃችን ይሰማ” ሥር የተሰባሰቡ ወገኖቻችን ይረዳሉ ብለን እናምናለን።

አርበኞች ግንቦት 7 ሙስሊም ወገኖቻችን ለዓመታት ያለመታከት ያካሄዱትን ትግል ያደንቃል። ከእንግዲህ ደግሞ እጅ ለእጅ ተያይዘን፤ ተደጋግፈን በመታገል ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ለሁላችንም የምትመች አገር እንድንገነባ ጥሪ ያደርጋል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

የፕሬዚዳንት ኦባማ የአፍሪካ ኅብረት ንግግርና እንደምታው

$
0
0

def-thumbየዩ ኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ሐምሌ 21 ቀን 2007 ዓም አዲስ አበባ ውስጥ በአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ያደረጉት ንግግር በርካታ ቁምነገሮችን የያዘ በመሆኑ አንጽዖት ሊሰጠው እንደሚገባ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
ፕሬዚዳንቱ በዚህ ንግግራቸው የአፍሪቃን በተለይም ደግሞ የአገራችንን ችግሮች ነቅሰው አሳይተዋል። ሰብዓዊ መብቶች ሰው በመሆናችን ያገኘናቸው በመሆኑ በቆዳችን ቀለም፣ በተወለድንበት አካባቢ፣ በምንናገረው ቋንቋ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያቶች ሊሸራረፉ የማይገቡ መሆኑን በመግለጽ “ሁላችንም እኩል ተወልደናል” በማለት ዘረኞችን አፍ የሚያዘጋ ኃይለቃል ተናግረዋል። “ሁላችንም ከአንድ ግንድ የበቀልን ነን፤ ሁላችንም አንድ ቤተሰብ ነን፤ ሁላችንም አንድ ጎሳ ነን” ካሉ በኋላ በዓለም ያለው አብዛኛው ችግር ይህንን መረዳት አለመቻላችን፤ ራሳችንን በእያንዳንዳችን ውስጥ ማየት አለመቻላችን ነው ብለዋል።

ይሁን እንጂ በብዙ የአፍሪቃ አገሮች፣ ዜጎች ነፃነታቸው የተገፈፈ መሆኑን፤ ምርጫ መኖሩ ብቻ ዲሞክራሲ ሰፈነ ማለት አለመሆኑ አብራርተዋል። ጋዜጠኞች፣ የተቃውሞ ፓለቲካ መሪዎችና ግንባር ቀደም ተሳታፊዎች፣ የሲቪክ እንቅስቃሴዎች መሪዎችን በእስር ቤት እያጎሩ ወይም በነፃነት እንዳይቀሳቀሱ እያደረጉ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አደረግን የሚሉ አገሮች መኖራቸው ለመግለጽ ኢትዮጵያን በዋቢነት ጠርተዋል።

ፕሬዚዳንት ኦባማ የሰላምና የደህንነት ጉዳይ ምን ያህል አሳሳቢ መሆኑን በሰፊው ከገለጹ በኋላ ለሰላም ሲባል ነፃነትን መንፈግ ሁለቱንም ሊያሳጣ የሚችል መሆኑም አስገንዝበዋል።
እድገትን በማፋጠን ዜጎችን ከድህነት ለማውጣት አዲስ አስተሳብ ያሻል፤ ለአዲስ አስተሳሰብ ደግሞ በነፃነት ማሰብ፤ ድምፃቸው የሚሰማ ዜጎች መኖር እና የሰብዓዊ መብቶች መከበር ቁልፍ ጉዳዮች መሆናቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል። የአፍሪቃ መሪዎች ሥልጣን ላለመልቀቅ የሚሄዱትን ርቀት በማንሳት ተሳልቀውበታል፤ ሙስናም የልማትና የመልካም አስተዳደር ፀር መሆኑን አስምረውበታል።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ፕሬዚዳንት ኦባማ ይኸ ቀራቸው በማይባል ሁኔታ በአህጉራችን በአፍሪቃ በተለይ በኢትዮጵያ የሰፈነው ክፉ አገዛዝ መተቸታቸው፤ ይህንን እዚያው የአፍሪቃ መዲና በሆነችሁ አዲስ አበባ ተገኝተው መናገራቸው በበጎ ይመለከተዋል። እሳቸው ያነሷቸውን ቁም ነገሮችን አድምጠው ማስተካከያዎችን የሚያደርጉ ገዢዎች ኑረውን ቢሆን ኖሮ የኛ ትግል ባላስፈለገ ነበር። ችግሩ መስማት እንጂ ማዳመጥና መተግበር የማያውቁ ገዢዎች የሰፈኑብን መሆኑን ነው።
ስለሆነም፣ አርበኞች ግንቦት 7: ፕሬዚዳንት ኦባማ በአፍሪቃ ኅብረት ንግግራቸው ሀቁን አብጠርጥረው በመናገራቸው የተሰማውን አድናቆት ይገልፃል፤ በዚሁ አጋጣሚ ደግሞ በንግግራቸው ያነሷቸው ቁምነገሮችን መደመጣቸውና በተግባር መተረጎማቸውን እንዲከታተሉ አበክሮ ይጠይቃል።

የፕሬዚዳንት ኦባማ ንግግር በሀቅ ላይ የተመረኮዘ በመሆኑ የህወሓት ሽማምንት የተከፉ ቢሆንም የኢትዮጵያን ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እውነታ የመቀየር ኃላፊነት የእኛው የኢትዮጵያዊያን ኃላፊነት መሆኑን በመረዳት፤ ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲና ለአገር አንድነት ግድ ያለን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ተባብረን አገራችን ከዘረኛውና ፋሽስታዊ ህወሓት አገዛዝ ነፃ የማውጣት ተጋድሎዓችን አጠናክረን እንድንቀጥል አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አለቃዎ ሳይሆን ቅን ህሊናዎ የሚያዝዎትን በመፈፀም መልካም ዜጋ ይሁኑ!

$
0
0

def-thumbመልካም ዜጋ ማለት ምን ማለት ነው?

ይህን ጥያቄ ለመመለስ በርካታ መጻሕፍት መፃፍ ይቻላል፤ መሠረተ ሀሳቡን ግን በጥቂት ዓረፍተ ነገሮች ማቅረብ ይቻላል።

መልካም ዜጋ ኢፍትሃዊ ተግባር ሲፈፀም “እኔ ምናገባኝ?” አይልም። መልካም ዜጋ “ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ”፤ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶም አይብቀል”፤ “እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም” እና በርካታ መሰል ምሳሌዎችን አይሰማም። መልካም ዜጋ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ቢሆን ከነፃና ቅን ህሊናው ጋር ታርቆ ይኖራል።

የህወሓት አገዛዝ፣ መልካም ዜጋ ማለት የመንግሥት ሥልጣን የያዘን ማንኛውም አካል ማክበርና በታማኝነት ማገልገል ተደርጎ እንዲተረጎምለት ይሻል። ፍትህ የሚያዛባ መንግሥትን መቃወም የመልካም ዜጋ አቢይ ተግባር መሆኑ የዘመናችን ወጣት እንዳይገነዘብ ያደርጋል። በተለይ ባለሙያዎች የሚያገለግሉትን አገዛዝ ባህርይ እግምት ውስጥ ሳያስገቡ የተቀጠሩበትን ሥርዓት በታማኝነት ማገልገል የዜግነት ግዴታቸው አድርገው እንዲወስዱት ይወተውታል።

ኦስካር ግሮኒንግ ( Oskar Groening)የዘጠና አራት ዓመት ሽማግሌ ጀርመናዊ ነው። በጀርመን የሂትለር አገዛዝ ወቅት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንፁሃን የተፈጁበት አሽዊትስ ካምፕ ውስጥ የሂሳብና ጽህፈት ሠራተኛ ነበር። ኦስካር ግሮኒንግ አንድም ሰው አልገደለም፤ አንድም ሰው አልገረፈም። እሱ ሂሳብ ነው የሠራው። ሆኖም በደል ሲፈፀም አይቶ “ምናገባኝ” ብሎ አልፏልና ከብዙ ዓመታት በኋላ ተከሶ በቅርቡ የ4 ዓመታት እስር ተፈርዶበት በሁለት እግሮቹ መቆም በማይችልበት በ 94 ዓመቱ በእርጅናውና በመጦሪያው ዘመን ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ፊት ተዋርዶ እስር ቤት ወርዷል።

በአንፃሩ ኦስካር ሽንድለር (Oskar Schindler) በጀርመን ናዚ ወቅት ሂትለር ይመራው የነበረው የናዚ ፓርቲ አባልና ሰላይ ነበር። ሆኖም ግን የሥርዓቱን ኢሰብዓዊነት ሲረዳ እዚያው የናዚ ፓርቲ ውስጥ ሆኖ አለቆቹ ያዘዙትን ሳይሆን ቅን ህሊናው ያዘዘውን በምስጢር መሥራት ጀመረ፤ በዚህም የ 1200 ሰዎችን ሕይወት ታደገ። ከጦርነቱ በኋላ ኦስካር ተከብሮ የኖረ በርካታ የክብር ስሞችና ሽልማቶች የተሰጠው በመልካም አርዓያነቱ የሚጠቀስ ሰው ሆነ።

በአገራችንም በአምስት ዓመታቱ የፋሽስት ወረራ ወቅት ስመ ጥር የውስጥ አርበኞች ነበሩ። ከነፃነት በኋላ ባንዶች እንኳን በውስጥ አርበኝነት ለመጠራት ያደርጉት የነበረውን እሽቅድድም ልብ በሉ።

በህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴግ፣ ደህዴግ እንዲሁም አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ ያላችሁ ወገኞች ኦስካር ግሮኒንግን ወይንስ ኦስካር ሽንድለርን መምሰል ትፈልጋላችሁ? በህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ውስጥ ያላችሁ ወገኖቻችን ነገ የምትዋረዱበትን ሥራ መሥራት ነው የሚበጃችሁ ወይስ ዛሬ ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ እየኖራችሁ ነገ ደግሞ ልጆቻችሁና የልጅ ልጆቻችሁ የሚኮሩበትን ተግባር መፈፀም ትፈልጋላችሁ? በአገዛዙ የስለላ ድርጅቶች ውስጥ ያላችሁ ወገኖች ስማችሁን በመልካም ማስጠራት አትሹምን?

ልቦና ያላችሁ ወገኖቻችን ሆይ! መልካም ዜግነት ሎሌነት አይደለም። መልካም ዜግነት ለቅን ህሊና ታማኝ መሆን ነው። መልካም ዜግነት ሲመች በገሀድ፤ ሳይመች በምስጢር ኢፍትሃዊነትን መዋጋት ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በማናቸውም መንገድ በአገዛዙ የፓለቲካ፣ የጦርና የፓሊስ ተቋማት፤ በስለላም ይሁን በሌላ የሲቪል ሙያ የተሰማራችሁ ወገኖቻችን የታዘዛችሁትን ሳይሆን ቅን ህሊናችሁ የሚጠይቃችሁን በመሥራት ኢፍትሃዊ፣ ፋሽስታዊና ዘረኛ የሆነውን የህወሓት አገዛዝን እንድታዳክሙ ጥሪ ያቀርብላችኋል። በአገዛዙ ውስጥ ሆናችሁ እያለም የምትሠሩት ለሀገርና ለትውልድ የሚጠቅም በርካታ ሥራ አለ። የአገዛዙን ምስጢራዊ ሰነዶች ለአርበኞች ግንቦት 7 እንዲደርስ ማድረግ፤ አሊያም በማኅበራዊ ሚዲያዎች (ለምሳሌ ፌስ ቡክና ቱተር) ማሰራጨት ትልቅ ዋጋ ያለ ሥራ ነው። የህወሓት ፀረ-አገር እና ፀረ-ሕዝብ ፕሮጀክቶችን ማሰናከል ሌላ ትልቅ ሥራ ነው። በነፃነት ታጋዮች ላይ የሚደረጉ ዱለታዎችን ማክሸፍ ሕይወት አድን ሥራ ነው። ድርጅቶቹ ውስጥ ሆኖ ድርጅቶቹን ማዳከም የመልካም ዜግነት ግዴታ መወጣት ነው።

በሥርዓቱ ውስጥ ሆነው ኢፍትሃዊነትን ለማጋለጥ እና ሥርዓቱን ለማዳከም ለሚጥሩ ወገኞች አርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ ክብር አለው፤ ደህንነታቸው እንዲጠበቅም የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል። ፀረ ኢትዮጵያ እና ፀረ ሰው የሆነውን የህወሓትን ሥርዓት ለመጣል እና በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲ፣ እኩልነትና የሀገር አንድነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከሥርዓቱ ውስጥም ውጭም የሚደረገውን ትግል እናፋፍም።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አርበኞች ግንቦት 7 በዋሽንግተን ዲሲ፣ በዳላስ እና በሲያትል የተሳካ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞችን አካሄደ

$
0
0

አርበኞች ግንቦት 7 ባለፈው ነሐሴ 10 2007 ዓ.ም በዋሽንግተን ዲሲ በሸራተን ሆተል ባካሄደው የተሳካ የገንዝብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ቁጥሩ በርካታ ኢትዮጵያዊ መገኘቱን ለማወቅ ተችሏ።

ንቅናቄው በመላው አለም በማካሄድ ላይ ባለው ተመሳሳይ ፕሮግራም በአውስትራሊያ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች በስደት ነዋሪ የሆነው ነጻነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በነቂስ በመሳተፍ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል በደጀንነት ለማገዝ ቁርጠኝነቱን እያሳየ ይገኛል።

በየክፍለ አህጉሩ በመደረግ ላይ ባለው ዝግጅት ወያኔ በብዙ ሚልዮን ዶላር ወጭ ከየመን አውሮጵላን ጣቢያ ጠልፎ የወሰዳቸው የቀድሞ ግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌና በቅርቡ የውህድ ድርጅቱን ለመምራት ወደ ትግሉ ሜዳ ያመሩት የንቅናቄው ሊቀመንበር የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ምስሎች ለጨረታ እየቀረበ በውድ ዋጋ መሸጣቸው ታውቋል።

የወያኔ አገዛዝ በህዝባችን ላይ የጫነውን ግፍና መከራ በማስወገድ አገራችን ውስጥ ፍትህ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነበት ዲሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የተጀመረውን ትግል የሚያግዝ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ ዝግጅቶች በቀጣዩ ሳምንታት በሰሜን አሜካ፡በካናዳና በአውሮጳ ከተሞች እንደሚደረጉ እየተነገረ ነው።

አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን የሃይማኖት አባቶች፣ አርቲስቶች፣ የፖለቲካ አክቲቪስቶችና የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪዎች ኢትዮጵያውያን በየዝግጅቶቹ ላይ በመገኘት ህዝቡን በማበረታታትና በማወያየት ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ ይገኛሉ።

AG7_5_16_08_2015

AG7_1_16_08_2015

AG7_2_16_08_2015

AG7_3_16_08_2015

AG7_4_16_08_2015

AG7_6_16_08_2015

AG7_7_16_08_2015

AG7_8_16_08_2015

AG7_9_16_08_2015

AG7_10_16_08_2015

AG7_11_16_08_2015

መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት !

$
0
0

def-thumbየግል ኑሮን ለማደላደል ሲባል የወያኔ አባል መሆን “ወይን ለመኖር” የሚል ስያሜ ከተሰጠው ዓመታት ተቆጥሯል። “ወይን ለመኖር” ዜጎች ነፃነታቸውን ለጥቅም አሳልፈው የሚሸጡበት፤ የሰው ልጅ ክብር የሚዋረድበት ገበያ ነው። በወይን ለመኖር “የገበያ ህግ” መሠረት እያንዳንዱ ዜጋ ሊያገኘው መብቱ የሆነውን አገልግሎት እንዲያገኝ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴግ፣ የደህዴግ፣ የአብዴፓ፣ የቤጉህዴፓ፣ የጋህአዴን፣ የሀብሊ ወይም የኢሶዴፓ አባል መሆን፤ አልያም መደገፍ ግዴታ ነው። እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች የህወሓት ተቀጽላ ወያኔዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ ያልሆነ እንኳስ የመንግሥት አገልግሎት ሊያገኝ ጥሮ ግሮ ያፈራውንም ይነጠቃል።

በዚህም ምክንያት፣ በገጠር ያለው አርሶ አደር ቁራጭ የእርሻ መሬት፣ የግብርና ባለሙያዎች የምክር እገዛ፣ የማዳበሪያና ዘር ግዢ፣ ብድር ወይም እርዳታ ለማግኘት በአካባቢው ባለ የወያኔ ድርጅት አባልነት መመዝገብ፤ አንድ ለአምስት መደራጀት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ የሚያራዝሙ ነገሮችን መሥራት ይጠበቅበታል። በከተሞች ውስጥም ሥራ ለመቀጠር፣ ለደረጃ እድገት፣ የመኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም) ለመግዛት ሲባል መወየን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ሆኗል:: በንግዱም ዘርፍ የንግድ ፈቃድ፣ የሥራ ቦታ እና የባንክ ብድር ለማግኝት፣ የመንግሥት ጨረታዎችን ለማሸነፍ፣ ከጉምሩክ እቃ ለማስለቀቅ፣ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት መወየን ግዴታ ነው።

“ወይን ለመኖር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ያዋረደ፤ ለትውልድ የሚተርፍ የማኅበራዊ ስነልቦና ኪሳራ ያደረሰ እና ደካማውን ወያኔን ጠንካራ በማስመሰል በሕዝብ የትግል መንፈስ ውስጥ ፍርሃትን የረጨ መሆኑ ግንዛቤ እየዳበረ በመጣ መጠን እየቀነሰ የመጣ ክስተት ነው። በአሁኑ ሰዓት ከቀድሞው እጅግ በተሻለ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ራሳችንን ከህወሓት ባርነት እያላቀቅን ምሬታችንን በግልጽ መናገር የጀመርንበት ወቅት ነው፤ ከዚያም አልፎ የህቡዕ ተግባራዊ የትግል እንቅስቃዎችን ማድረግ ደረጃ ላይ ደርሰናል።

አገር ውስጥ እየተዋረደ የመጣው “ወይን ለመኖር” በአገዛዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካይነት በውጭ አገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን (ዲያስፓራ) መካከል ነፃነታቸውን በጥቅም የሚለውጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ፍለጋ ተሠማርቷል። አገዛዙ ተስፋ ያደረገው ያህል ባይሆንም ጥረቱ የተወሰነ ውጤት እያስገኘለት ነው። በጥቅማ ጥቅም እየደለለ ካመጣቸው ውስጥ በስርዓቱ ብልሹነት ያዘኑና የተሰማቸውን በግልጽ የተናገሩ መኖራቸው የሚያስደስትና የሚያበረታታ ቢሆንም ከመንደር ካድሬዎች ባነሰ ተለማማጮችና አጎብዳጆች በማየታችን ተሸማቀናል። ኢትዮጵያ ውስጥ ካለነው አብዛኛው ሕዝብ አንፃር ሲታይ በተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙት ዲያስፓራዎች መካከልም ነፃነታቸውን በጥቅም ለመለወጥ የሚፈቅዱ መገኘታቸው አሳዛኝ ነው። እነዚህ ክብራቸውን በጥቅም የለወጡ ዲያስፓራዎች ዓለም ባንክንና የዓለም የገንዘብ ድርጅትን (IMF) ተክተው ህወሓት ስላስገኘው ፈጣን እድገት በአገዛዙ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ሲነግሩን መስማት ያሳፍራል። የህወሓት አገዛዝ “ፍትህን፣ መልካም አስተዳርንና ዲሞክራሲን አስፍኗል፤ ይህንንም መጥተን በዓይኖቻችን ተመልክተናል” እያሉ የግፉን ገፈት እየቀመስን ላለነው ሲነግሩን መስማት ያማል።

እነዚህ ወገኖቻችን ህወሓትን በማሞካሸት የሚያገኙት መሬት ብዙ ድሆች የተፈናቀለቡት፤ ለእነሱ በብላሽ የተሰጠው ብድር በረሃብ ለሚጠቃ ወገን የተላከ እርዳታ መሆኑ ማሳሰብ ይገባል። ከህወሓትና አጫፋሪዎቹ ጋር ተስማምተው ባገኙት ገንዘብ የሚቆርሱት እያንዳንዱ እንጀራ የብዙ ወገኖቻችን ደምና እንባ የፈሰሰበት መሆኑ ማስገንዘብ ያሻል። ከህወሓት ጋር በማበር በወገኖቻችን ድህነትና ችጋር እየከበሩ ያሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት ከዚህ እኩይ ሥራቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቅ ይገባል። እኚህ ወገኖች የራሳቸው ክብር ማጉዳፋቸውን ብቻ ሳይሆን የልጅ ልጆቻቸውም የሚያፍሩባቸው መሆኑን ማስታወስ ይገባል። ከዚህም አልፎ የዛሬ ተግባራቸው ነገ በህግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑን ሊያውቁ ይገባል።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የአገዛዙን እድሜ በማራዘም ላይ የተሰማሩ፤ በድሆች ድህነት ለመክበር በመሯሯጥ ላይ ያሉ፤ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ለአገዛዙ ጥብቅና የቆሙ የዲያስፓራ አባላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳስባል።

አርበኞች ግንቦት 7 “ከህወሓት ውድቀት በኋላ ያለው ጊዜ ለእናንተም ከዛሬው የተሻለ ይሆናል። ዛሬ ከህወሓት ጋር ያላችሁን ሽርክና አቋርጡ። ለነፃነት የሚደረገውን ትግል እርዱ፤ መርዳት ባትችሉ እንቅፋት አትሁኑ፤ አለበለዚያ ግን ከተጠያቂነት የማታመልጡ መሆኑን እወቁ” ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!! !


ረሀብን ለማጥፋት ህወሓትን ማስወገድ

$
0
0

def-thumbረሀብ በአገራችን ላይ እያንዣንበበ ነው። በአፋርና በሱማሌ ከከብቶች አልፎ ሕፃናት እየሞቱ ነው። የረሀቡ አደጋ ወደ ኦሮሚያና ሌሎች የደቡብ ገጠሮች እየተዛመተ ነው፤ ሰሜን ኢትዮጵያም ከአደጋ ውጭ አይደለም።

“ከአስር ዓመታት በላይ በተከታታይ በየዓመቱ ከአስር በመቶ በላይ የኢኮኖሚ እድገት አሳይተናል” የሚለው ዓይን ያወጣ ውሸት፤ “ድህነትን ተረት እናደርጋለን” የሚለው ጉረኛ መፈክር፤ “መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ተርታ እንደርሳለን” የሚለው ባዶ ተስፋ፤ የወያኔዎችና ጀሌዎቻቸው በፎቅና ቪላዎች መንበሽበሽ፤ የድግሶችና የስብሰባዎች መብዛት ለሕዝባችን ቁርስ፣ ምሳና እራት አልሆኑም።

አገዛዙ ጉራውና ባዶ ተስፋ መስጠቱ እንዳለ ሆኖ የረሀቡን ምክንያት በተፈጥሮ ላይ ማላከኩን ተያይዞታል። ለመሆኑ ተፈጥሮ ብቻውን እየተደጋገመ ለሚመጣ ችጋርና ቸነፈር በቂ ምክንያት ሆኖ ያውቃልን? አስከፊ የረሀብ ዜናዎች የሚሰማባቸው አገሮች በሙሉ ነፃነት የታፈነባቸው አገሮች መሆናቸው የአጋጣሚ ጉዳይ ነውን? ለምንድነው አንድ ዓይነት ችግር እየተደጋገመብን መላ መፈለግ ያቃተን? መልሱ አጭርና ቀጥተኛ ነው። “ችግር የመሳካት እናት” የምትሆነው በነፃነት ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ሲኖር ነው። በባርነት ጨለማ ውስጥ ያለ ጭንቅላት ለችግሮች መፍትሄ የማፍለቅ አቅም የለውም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነቱ ድኩም ጭንቅላት ችግሮችን ማሸነፍ ሳይሆን ተሸናፊነትን ተቀብሎ ከችግሮች ጋር ተስማምቶና ተወዳጅቶ መኖርን ይመርጣል። ነፃነት ያለው ሕዝብ ረሀብን እንደሚያሸነፍ ተደጋግሞ የታየ ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው ረሀብን የተፈጥሮ ሚዛን መዛባት ውጤት ብቻ አድርጎ ማቅረብ እውነትን መሸፈጥ የሚሆነው። ረሀብ የብልሹ አስተዳደር ውጤት ነው።

አገራችንን የረሀብ ቀጠና ካደረጉ የ24 ዓመታት የህወሓት “ድሃን ዘርፈህ ብላ” የኢኮኖሚ ፓሊሲ ውጤቶች መካከል አንዳንዱን ለአብነት ያህል መዘርዘር ይቻላል።

1. ገበሬና መሬት ተለያይተዋል። ለም መሬቶች በኢንቨስትመንት ስም በዘመኑ የህወሓት ጉልተኞች በመያዛቸውና እነሱ ደግሞ በተራቸው ለባዕዳን እየሸጡ በመሆኑ ባለሀገሩ ጭሰኝነት እንኳን አጥቶ ለቀን ሠራተኝነትና ልመና ተዳርጓል። አዳዲሶቹ ባለሃብቶች ለፈጣን ኪስ መሙላት እንጂ ለዘለቄታ የአፈር ልማት ፍላጎቱም እውቀቱም የላቸውም። በዚህም ምክንያት ገበሬው ትንሽ የዝናብ ዝንፈት እንኳን መቋቋም እስከማይችልበት ደረጃ ተዳክሟል።

2. በዘር ላይ በተመሰረተ ክልላዊ ድንበር ሳቢያ ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች በአገራቸው ውስጥ ተዘዋውረው መሥራት አልቻሉም። ከሰሜን ወደ ደቡብ ከተሰደደ የአገራችን አርሶ አደር ይልቅ ለቻይና ገበሬ መሬት ማግኘት ይቀለዋል። እንዲያውም ኢትዮጵያዊው ድሀ ገበሬ በዱላ ሲባረር፤ ከውጭ አገር የመጣው ቱጃር ገበሬ ብድርና ማበረታቻዎች ይሰጠዋል።

3. ደኖቻችን ተጨፍጭፈው፣ ለም መሬታችን ተሸርሽሮ በማለቁ የግብርናችን ምርታማነት በእጅጉ ቀንሷል። በዘመነ ወያኔ የደን ጭፍጨፋና የመሬት መሸርሸር በአስደንጋጭ ሁኔታ ጨምሯል። አገሪቷ በፍጥነት ወደ ምድረበዳነት እየተቀየረች ነው።

4. ፋይዳ ያለው የስነ ሕዝብ ፖሊሲ ባለመኖሩ የሕዝብ ብዛት አሻቅቧል። እንደ ኢኮኖሚው ሁሉ ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ብዛት ሊቆጣጠር የሚሞክረው ቢሮ ውስጥ ቁጭ ተብሎ በሚደረግ የቁጥር ጨዋታ ነው። የስታተስቲክሱ ባለሥልጣን ቁጥራችንን በትክክል ሊነግረን ባይፈልግም እንኳን ረሀብ መብዛታችንን እየነገረን ነው።

5. የህወሓት ባለሥልጣኖችና በየክልሉ ያደራጇቸው ምስለኔዎች ራሳቸውን ባለሚሊዮኖች አድርገዋል። እነዚህ በአንድ ጀምበር የበቀሉ ቱጃሮች ከገንዘብ በተጨማሪም የጄኔራልነት፣ የሚኒስቴርነት፣ የክልል ገዢነት፣ እጅግ ቢያንስ የቢሮ ኃላፊነት ሥልጣንን ኪሳቸው ውሰጥ ከተዋል፤ ልባቸው የተመኘውን ዲግሪ ሸምተዋል። የመንግሥት ሥልጣንና ሃብት ይኸን ያህል የተቆራኙበት ሥርዓት በኢትዮጵያ ኖሮ አያውቅም። የጥቂቶች ያለአገባብና ያለቅጥ መክበር በአንፃሩ ደግሞ የብሃኑን ሕዝብ መደህየት ድህነትን መዋቅራዊ አድርጎታል።

6. በአቋራጭና በፍጥነት ለመክበር አስተማማኙ መንገድ የገዛ ራስ ጥረትና ታታሪነት ሳይሆን ቅጥፈት፣ አጭበርባሪነትና ሎሌነት መሆኑን የወያኔ ካድሬዎች በተግባር እያሳዩ ጥሮ ማደርን “ኋላ−ቀር አሠራር” አድርገውታል። በህወሓት የኢኮኖሚ ፓሊሲ የተበረታቱት አድርባይነት፣ ስንፍናና እና ልመና ችግርን የመጋፈጥ አቅማችንን ሰልበውታል።

እነዚህና የመሳሰሉት ጭብጦችን በማንሳት የረሀቡ መሠረታዊ ምክንያት የህወሓት አገዛዝ እንጂ ተፈጥሮ አለመሆኑን አስረግጠን እንናገራለን። ሕዝባችን በነፃነት ማሰብ፣ መመራመር፣ መፈተሽ ቢችል ኖሮ ረሀብን ማጥፊያ ብልሃት ማግኘት ባላቃተውም ነበር። ወደፊትም ቢሆን ተፈጥሮ እኛ እንደፈለግናት አትሆንም፤ መተማመኛችን የሰው ልጅ ወሰን የለሽ የፈጠራ ችሎታና ችግሮችን የመፍታት አቅም ነው። ለዚህ ደግሞ ችግሮችን በልጦ መገኘት ያስፈልጋል። ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከችግሮች በታች ሆኖ መፍትሄ ከአገዛዙ የሚጠብቅ ደካማ እንዲሆን አድርጎታል። በዚህም ምክንያት ነው የችግሮቻችን ቁንጮ ራሱ ወያኔ ነው የምንለው።

ህወሓትን ከመንግሥት ሥልጣን ሳናስወግድ ድህነትንና ረሀብ እናስወግዳለን ማለት ዘበት ነው:: ድህነት የህወሃት ዋነኛ የገቢ ምንጭ በመሆኑ ህወሓት ሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ በወሬ ካልሆነ በስተቀር ድህነት በተግባር ሊቀጭጭ አይችልም። ችጋርና ህወሓት እጅና ጓንት ናቸው። ረሀብ የህወሓት ባለውለታ ነው። ረሀብ የህወሓት የቁርጥ ቀን አጋሩ ነው። ህወሓት በረሃ እያለ በአሸዋ የተሞሉ ጆንያዎችን እህል አስመስሎ በመሸጥ ለእርዳታ በመጣ ገንዘብ ራሱን አደራጅቷል። ስልጣን ከያዘም በኋላ “ረሀብን እየተዋጋሁ ነው” በማለት የምዕራባዊያንን ድጋፍ ለማግኘት ጠቅሞታል። ረሀብና ችጋር የወያኔ “ጪስ አልባ” እንዱስትሪዎች ናቸው። ሕዝባችን ተራበ ማለት የወያኔ ኩባንያዎች ሥራ አገኙ ማለት ነው። ህወሓት ረሀብን ለመቀነስ ቅንጣት ታህል ፍላጎት ቢኖረው ኖሮ በዚህ ወር ውስጥ በተደረጉ ስብሰባዎች በወጣው ወጪ ብቻ በአገራችን ላይ ያንዣበበውን ረሀብ በቁጥጥር ማዋል በተቻለ ነበር።

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለወገኖቻቸን መራብ ተጠያቂው የህወሓት ዘረኛ አገዛዝ ነው ይላል። ረሀብን ከኢትዮጵያ ምድር ለዘለቄታው ለማስወገድ የህወሓት አገዛዝን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ደህንነት የቆመ፣ በሕዝብ የተመረጠ እና ከሕዝብ አብራክ የወጣ መንግሥት እንዲኖረን እንታገል ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

መልካም አዲስ ዓመት –ድጋፍ ለአገር አድን ንቅናቄ

$
0
0

def-thumb“የኢትዮጵያ አገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ” ምስረታ ዜና በአዲስ ዓመት መባቻ መሰማቱ ትልቅ የምሥራች ነው። ይህንን ንቅናቄ ለመመስረት ከፍተኛ ጥረት ያደረጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ምስጋና ይገባቸዋል።

የኢትዮጵያ አገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ መመስረት የህወሓት አገዛዝን ተጋግዞ ለመጣል ከማስቻሉም በላይ ድሉ የአንድ ወይም የጥቂት ድርጅቶች ድል ከመሆን ይልቅ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድል እንዲሆን ያስችላል። ከዚህም በተጨማሪ ከህወሓት አገዛዝ በኋላ የተባበረች ኢትዮጵያ እንደምትኖረን ማስተማመኛ ከሚሰጡን ነገሮች ዋነኛው ዛሬ የምናደርጋቸው ትብብሮች ናቸው። የአገር አድን ንቅናቄ ዛሬ የምናደርገውን ትብብር መዋቅራዊ ገጽታ የሚሰጠው እና ዘለቄታነት እንዲኖረው የሚያግዝ በመሆኑ ለአገራችን ለኢትዮጵያ እና ለሕዝቧ የሚሰጠው ጥቅም ዘርፈ ብዙ ነው።

የአንድን ድርጅት ጥንካሬ ከሚወስኑ ነገሮች ዋነኛው የአባላቱና ደጋፊዎቹ ጥንካሬ ነው። የአገር አድን ንቅናቄም ጥንካሬ ከሚወስኑት ነገሮች ዋነኛው አባላትና ደጋፊው ናቸው። የአገር አድን ንቅናቄ እንዲጎለብት የምንመኝ ሁሉ ለንቅናቄው መጠናከር የምናበረክተው አስተዋጽኦ አለ። ከሁሉ አስቀድሞ ኢትዮጵያ አገራችን ከግዛቷ ውስጥ የሚገኙ ማኅበረሰቦች ሁሉ አገር መሆኗን እና እያንዳንዱ ማኅበረሰብ ከሌላው ጋር እኩል መብት ያለው መሆኑን መቀበልና በተግባርም ማሳየት ይገባል። እያንዳንዱ ዜጋ እና እያንዳንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ከሌሎች ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር በጋራ አገራችን የማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆን ሁኔታዎችን ማመቻቸት ያስፈልጋል። በምናደርጋቸው ፓለቲካዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ የዜጎችና የማኅበረሰቦች በእኩልነት መሳተፍ እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን ተረድተን መንቀሳቀስ ይኖርብናል። ለህወሓት “ከፋፍለህ ግዛ” ፓሊሲ መመቸት የለብንም። በዘር፣ በሃይማኖት፣ በጾታ፣ በእድሜም ሆነ በቋንቋ ሳንከፋፈል የጋራ ትኩረታችንን የጋራ ቤታችን የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳን ላይ እናድርግ።

በኢትዮጵያ፣ በዳር አገር እና በውጭ አገራት የሚገኙ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች ከሕይወት መስዋትነት ጀምሮ በጊዜዓቸው፣ በገንዘባቸውና በእውቀታቸው ንቅናቄዓቸውን ሲረዱ ቆይተዋል። በአሁኑ ሰዓት በበርካታ የዓለም ከተሞች እየተደረጉ ያሉት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻዎች የሚያመለክቱት የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች ምን ያህል የነፃነት ትግሉ የጀርባ አጥንት መሆናቸው ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 ይህ ድርጅታዊ ፍቅርና ተነሳሽነት ወደ አገር አድን ንቅናቄውም እንዲሸጋገር ይሻል።ከአሁን በኋላ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላት እና ደጋፊዎች የአገር አድን ንቅናቄውን የማጠናከር ኃላፊነት አለባቸው። በዚህም ምክንያት የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች በሚያደርጓቸው የትግል እንቅስቃሴዎች ሁሉ የሌሎች ዲሞክራሲያዊ የኢትዮጵያ ኃይሎች ተሳትፎ እንዲኖርበት ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ሕዝብን የማስተባበር ሥራ በሁሉም ቦታዎችና በሁሉም እርከኖች መሠራት ይኖርበታል። ይህ የሁለገብ የትግል ስትራቴጂዓችን አንዱ አካል በመሆኑ አባላት ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያሳስባል።

አርበኞች ግንቦት 7 ለአባላቱና ደጋፊዎቹ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ “እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን፤ አዲሱ ዓመት የድል ዓመት እንዲሆንልን በጽናት እንታገል” ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ከአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

መስከረም 3 ቀን 2008 ዓ.ም

def-thumbበኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ የፖለቲካ ትግል ታሪክ ውስጥ ባጠቃላይና በተለይ ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የፖለቲካ ስልጣኑን በተቆጣጠረባቸው ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ውስጥ ህወሓት/ኢህአዴግን እንቃወማለን በሚለው ወገን ገንነው የመጡ ሁለት አፍራሽና ኋላቀር የፖለቲካ አዝማሚያዎች (trends ) አሉ። ከነኝህ ውስጥ አንደኛው ራስን በፖለቲካ አመለካከት ዙሪያ ከማሰባሰብ ይልቅ በጎጥና በዘውግ ደረጃ የመመልከትና ሀገራዊ ፖለቲካን በደም ቆጠራ የመመንዘር አባዜ ነው። ሁለተኛውና ከዚሁ ያልተናነሰው ችግር የፖለቲካ ድርጅት በመሰረታዊ ያመለካከት መርሆች ዙሪያ ሰፋ ያለ የማህበረሰብ ክፍልን የማሰባሰቢያ ድንኳን መሆኑ ቀርቶ፤ በስራ ሳይሆን ድንገተኛ አጋጣሚን በመጠበቅ ትርፍ ለማጋበስ በሚቋምጡ ሰነፍ “ነጋዴዎች“ የተቋቋሙ ሩቅ የማይሄዱ የንግድ ድርጅቶች ይመስል በተግባር ምንም የማይፈይዱ ”የፖለቲካ ድርጅቶች“ እንደ አሸን የመፍላታቸው ፈሊጥ ነው። እነኝህ ሁለቱም አዝማሚያዎች የህወሓት/ኢህአዴግን ህይወት ከማራዘም አልፈዉ ማህበረሰቡን ወደሚመኘው እውነተኛ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት አንድ ጋት እንኳን ፈቀቅ አላደረጉትም። ይልቁንም ዴሞክራሲን የሚናፍቁ ታጋዮች ተሰባስበውና ተጠናክረው ስርዓቱን ከመግፋት ይልቅ በግለሰብ ደረጃ ወይንም በትናንሽ ቡድኖች በመሰባሰብ የሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች በስርዓቱ በቀላሉ እየተመቱ ብዙ ታጋዮች ለሞት፤ ለስቃይና ለእስር ተዳርገዋል። አሁንም እየተዳረጉ ነው።

የዚህ አይነት የትግል አካሄድ ሩቅ እንደማያስኬድ የኢትዮጵያ ህዝብ ከተገነዘበው ቆይቷል። ይህ አካሄድ እንዲቀየርና የፖለቲካ ሀይሎች ተሰባስበው ይህንን በስልጣን ላይ ከሚገባው በላይ የቆየና አገሪቱን ለውርደት የዳረገ የጥቂት ዘራፊዎች ቡድን ከጫንቃው ላይ እንዲያነሱለት ሲማጠን ቆይቷል። ምንም እንኳን በመሪዎች ድክመት የሚመኘውን ዳር መድረስ ባይችልም ባጭር ጊዜ ልምዱ በትንሹም ቢሆን የተባበረ ትግል ሊያስገኝ የሚችለውን ጥቅም በመጠኑም ቢሆን አይቶታል።

ይህ የህዝብ ፍላጎት መኖር ግን በራሱ ይህንን የተባበረ ሰፊ ማህበራዊ እንቅስቃሴ መፍጠርን ቀላል ያደርገዋል ማለት አይደለም። በብዙ ስራ፤ በብዙ ድካምና ያላሰለሰ ጥረት የሚፈጠር እልህ አስጨራሽ ሂደት ነው። ባንድ በኩል እንዲህ አይነት ሰፊ የህዝብ እንቅስቃሴ በስልጣኑ ለመቆየት የሚፈጥርበትን ችግር የሚረዳው በስልጣን ላይ ያለው የዘራፊዎች ቡድን ይህን እንቅስቃሴ ከወዲሁ ለማምከን ያለ የሌለ የገንዘብ፤ የስለላና የተንኮል ሀይሉን ይጠቀማል። በተቃዋሚ ድርጅቶች ውስጥ ሰርጎ በመግባትና ደካማ ሀይሎችን በገንዘብ በመግዛት ወይንም በማስፈራራት እንዲህ አይነት ትብብሮች እንዳይፈጠሩ ከውስጥ ለመቦርቦር ተግቶ ይሰራል። በሌላ በኩል ደግሞ የትም የማያደርሳቸውን “የራሳቸውን ድርጅት” የሙጢኝ ብለው ለትልቅና አገራዊ አላማ እራሳቸውን ላለማስገዛት የቆረጡ ደካማ “የድርጅት መሪዎች” እንዲህ አይነቱን የጋራ እንቅስቃሴ በራሳቸው ግብዝነትና ስግብግብነት ምክንያት ብቻ ሊያሰናክሉት መሞከራቸው አይቀርም።

ይህ ግን ጊዜው ያለፈበት አዝማሚያ ነውና የሚሳካ ሙከራ አይሆንም። የተናጠል ትግል ሂደት ማብቂያው ጊዜ ተቃርቧል። የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ የሚታገሉ ኃይሎች እንዲህ አይነቱን ፋይዳ ቢስ ሂደት የመቀበል ትዕግስታቸው ተሟጧል። በቅርብ ጊዜ የሞላ አስገዶምን መክዳት በማስመልከት የትህዴን አመራር ባወጣው መግለጫ “ኢትዮጵያን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊት ሀገር ለማድረግ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ጋር አብሮ መስራት የድርጅታችን መሰረታዊ መርሆ ነው” እንዳለው ይህ መሰረታዊ መርሆ በሀገራችን የጸረ ህወሓት/ኢህአዴግ ትግል የበላይነት ይዞ እየመጣ ያለ እጅግ አስፈላጊና ለድሉም ወሳኝ የሆነ የጊዜው የፖለቲካ አዝማሚያ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ይህን መሰረታዊ መርሆ ከምር ወስዶ የሚንቀሳቀስ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ነው።

ይህ አዲስ የፖለቲካ አዝማሚያ ምቾት የማይሰጣቸው የፖለቲካ ኃይሎች መኖራቸው የሚጠበቅ ነው። የህወሓት/ኢህአዴግ የስለላ ድርጅት ከሰሞኑ ሞላ አስገዶምን በማስመልከት ባወጣው መግለጫ በግልጽ እንዳስቀመጠው ኢትዮጵያውያን የዴሞክራሲ ኃይሎች ተሰባስበው እንዳይታገሉና ስርዓቱን እንዳይፈታተኑ የማያደርገው ጥረት የለም። በዚህ በህወሓት/ኢህአዴግ መሰሪ እንቅስቃሴ ደግሞ በቀላሉ መጠቀሚያ የሚሆኑት በጋራ የሚደረግ ትግል በግለሰብ ደረጃ ያሳጣናል ብለው የሚፈሩት “የግል ጎጆና” ጥቅም የሚያስጨነቃቸው ደካማ የፖለቲካ መሪዎች ነን ባዮችን ነው። ባንጻሩ በየድርጅቶቹ ውስጥ በሚገኙት ብዙሀኑ ሩቅ አሳቢ መሪዎች ጥረትና በተለይም ደግሞ ይህን ትግል ለአላማ እንጂ ለሌላ ምንም አይነት የግል ጥቅም ያልተቀላቀሉና በትግሉ ሂደትም ትልቁን ሚና በሚጫወቱት ብዙሀን ታጋዮች አልበገር ባይነት እንዲህ አይነት ደካማ መሪዎች ተከታይ በማጣት ሲዳከሙና በሚያደርጉት እንቅስቃሴ በድርጅታቸው ውስጥ የሚነሳባቸውን ተቃውሞ መቋቋም ባለመቻላቸው በቀላሉ እየተፍሸለሸሉ ከመራገፍ በስተቀር በድርጅቶቹ ላይ ከባድ ጉዳት ሳያደርሱ ይከስማሉ።
በህወሓት/ኢህአዴግ “የስለላ ድርጅት አቀናባሪነት” በሞላ አስገዶም መሪነት ከሰሞኑ የተሞከረው የማፍረስ ንቅናቄ ከሽፎ ወደ ተስፋ መቁረጥ የክህደት እንቅስቃሴ የተቀየረው የሰሞኑ ሙከራም የዚህ አጠቃላይ ሂደት አካል ነው። በዚህ የከሸፈ ሙከራ ውስጥ እጅግ የሚገርመውና የትህዴንን ብዙሀን አመራሮች ብስለት፤ የድርጅቱን መዋቅራዊና ድርጅታዊ ጥንካሬ፤ እንዲሁም ብዙሀኑ ታጋይ ለጋራ ትግል ያለውን ቆራጥ አቋም ያስመሰከረው፤ ይህንን የማፍረስ ሙከራ የመራውና ሳያሳካለት በመጨረሻም በጣም ጥቂት ተከታዮቹን ብቻ ይዞ የከዳው ለረጅም ጊዜ የድርጅቱ ሊቀመንበር የነበረው ሞላ አስገዶም መሆኑ ነው። እንዲህ አይነት የመክዳት ሂደት ባጭር ጊዜ በማህበረሰባችን ላይ የሚፈጥረውን አስጨናቂ ስሜት የምንረዳው ቢሆንም ከዚያ በላይ ልንረዳው የሚገባው ግን በእንዲህ አይነት ከፍተኛ ያመራር ቦታ የነበረ ሰው ሙከራ አለመሳካት በእርግጥም የሀገራችን ፖለቲካ እየበሰለ፤ ከግለሰብ አመራሮች ተጽእኖ እየተላቀቀ፤ አዲስ የተባብሮ መታገል አቅጣጫን እያበሰረ እየሄደ መሆኑንና በትናንሽ ሰዎች መግተርተር ይህ ሂደት የማይቀለበስ መሆኑን የሚያመለክት የረጅም ጊዜ ግኝት መሆኑን ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ አጋጣሚ ለትህዴን ብዙሀን አመራርና ለሰፊው ታጋይ በመርህ ላይ ለተመሰረተው አቋማቸውና መርሃቸውን ለማስጠበቅ ለሚያደርጉት ቆራጥ ትግል ያለውን ጓዳዊ አክብሮት ይገልጻል። በመግለጫቸው ላይ በግልጽ ያስቀመጡት መርሆአቸው የኛም መርሆ መሆኑን ስንገልጽላቸው በታላቅ ኩራት ነው። ድርጅታቸውን እያጸዱ የተመሰረቱበትን መርሆ ጠብቀው ለመጓዝ ባሳዩት ቁርጠኝነትና ወደፊትም በሚያደርጉት ትግል ምንጊዜም ከጎናቸው መሆናችንንና ጓዳዊ ድጋፋችን ምንጊዜም እንደማይለያቸው በዚህ አጋጣሚ ደግመን ልናረጋግጥላቸው እንወዳለን። በመግለጫቸው ላይ እንዳሉትም ይህ ትግል ኢትዮጵያን ዴሞክራሲያዊ ሳያደርግ የማይቆምና እንዲያውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለኢትዮጵያ ህዝብም በየጊዜው በሚፈጠሩ እንቅፋቶች ላይ ሳያተኩር ትግሉን በሙሉ ልብ እንዲደግፍ ያደረጉት ጥሪ የኛም ጥሪ ነው።

አንድነት ኃይል ነው!!!
አርበኞች ግንቦት 7: ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia

$
0
0

logo-timeret
United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia, (pdf)

Ethiopia is one of the oldest nation-states in the world. Both written and oral history and recent archeological discoveries, despite regional rivalries, suggest the historical continuity of the nation. It was a Monarchy until 1974. From 1974 to 1991 the country was declared to be ‘Peoples Democratic Republic’ by the military junta, Derg, and went through a traumatic experience. Tigrai Peoples Liberation Front (TPLF), a guerrilla force from a minority ethnic group that led the rebellion against the military junta and captured the institutions of the State, has been in power for the past 24 years. The country is ruled as a one-party state under a façade of multi-party system since 1991.

The state is characterized by an intensifying political repression, rampant economic corruption, denial of basic human and political rights and repeated sham elections. The top brass of the army and security organs of the state, including key diplomatic positions, are effectively mono-ethnic despite the claim of the regime to stand for the equality of all ethnic groups. The people have completely lost confidence in the government after the regime shamelessly declared itself to have won 100% of the parliamentary seats in the 2015 election. Ethiopians, with no other choice available to them for democratic transition, have now risen up in arms. And this is a credible threat of force to the regime. History has time and again proven that no government that denies freedom, justice and democracy to its people will not survive their wrath.

Against this background, Ethiopian democratic forces, reflecting the broad diversity of the Ethiopian society, have recently formed the United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED) as an umbrella organization. UMSED is committed to coordinate the people’s struggle for effective resistance against TPLF’s tyranny and to ensure the transition to true democracy and stable political order in Ethiopia. No one relishes the idea of armed conflict; but, there are times when armed self-defense becomes the only choice to resist the unbearable violence by minority against majorities and to bring about an enduring peace and stability in a society.

Ethiopians have given up on elections as they have become meaningless rituals: There have been five national elections under the TPLF. The first election in 1995 resulted in 3 opposition members being elected to the parliament that has a total of 548 MPs. In the second election of 2000, the number for the opposition members rose to 27. In the 2005 general election, which was monitored by the Carter Center, European Union and other observers, Ethiopians turned out in record numbers and voted for the opposition, mainly CUD and UEDF. The results were rigged; and the election was blatantly stolen. Furthermore, many unarmed and defenseless peaceful protesters demanding the respect for the vote of the people were indiscriminately gunned down in a broad daylight. Leaders of opposition political parties, civic societies, journalists and dignified and well-meaning Ethiopian citizens were jailed for two years. Members of the fact finding commission appointed by the government itself published the evidence that the government has cold-bloodedly massacred 197 Ethiopians on this day of infamy. Today, these fact finders are themselves in exile fleeing for their lives. Only one opposition member was able to win a seat in the parliament during the 2010 fourth national election. In the most recent election of May 2015, in which the regime claimed 100% landslide victory of all parliamentary seats, no credible outside/international observers, excepting those from the corrupt African Union, were allowed to monitor the election.

The Ethiopian government owns all land in the country, including most residential and commercial real estate in towns and cities like all other communist totalitarian regimes in the world. The industrial and service sector of the economy is also heavily controlled by Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT), an endowed conglomerate parastatal serving as a front for the ruling TPLF party. Until recently it was managed by the wife of the late Prime Minister. Both were members of the TPLF/EPRDF politbureau and the legislative assembly, making their work similar to the work of the late Romanian dictators, Nicolae Ceaușescu and his wife Elena Ceaușescu. The total grip on land and the economy is a source of much power to the regime and the accompanying oppression of the people in a country where eighty five percent of the population is engaged in farming and most city dwellers rely on the government for employment and housing. All land in the country was declared government property by the old communist military regime and the current regime has continued the practice. The monopolization of land by the TPLF and its surrogate administrators has been the source of wealth for some, but continued to stifle the production of food as in the communist era. Thanks to this land policy, today lives particularly that of children and cattle in the Afar, Amara, Gambella, Somali and Southern regions of the country are perishing due to a single season rainfall failure.

Ethiopians are tired of their voices being totally muffled: Independent media is not tolerated. The International Federation of Journalists has declared the regime to be one of the worst offenders of press freedom. Television, Internet, and major print media is owned and operated by the government. The state is the only Internet Service Provider and uses Chinese, Italian and British Internet hacking and intercepting technology vendors to spy, trap and intimidate its critics and opponents. The regime also spends precious resources on signal jamming technology to stop the free flow of information from the outside. Foreign based and independently operated radio and TV broadcasts by the Ethiopian Diaspora are jammed on regular basis as are broadcasts in Ethiopian languages by Voice of America and Deutsche Welle Radio.

Ethiopians can no longer tolerate an entrenched ethnic minority rule: The TPLF, the dominant party in the coalition known as Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), controls all aspects of life in the country, similar to apartheid South Africa, by installing its ethnic rulers as heads of major institutions across the entire state apparatus. Ethiopians and international observers including those who bend backwards to “apologize” for the regime know very well that ethnic Tigrayans control the army, security services, telecoms , foreign affairs, and other nerve centers of the Ethiopian state machinery. The TPLF party pits different ethnic and religious groups against one another simply to perpetuate its minority rule and monopoly on resources. The regime has no respect for religious freedom. It has created chaos in both the Ethiopia Orthodox Tewahido Church and the Muslim mosques by interfering in the administration of their purely religious institutions through its political cadres. It has similar surrogates in Pentecostal Churches. Religious leaders who resist this interference are exiled (as the Orthodox Christian leaders) and imprisoned (as the Muslim community leaders). Ethnic minority domination has become a source of stress on the harmony of the people that is essential for peaceful coexistence in a diverse mutli-ethnic and multi-religious country like Ethiopia.

Ethiopians have said enough to the regime’s oppression with impunity: In the last twenty four years, the people have been appealing to the regime to respect the fundamental political and civil liberties of the citizenry. Peaceful protests are disallowed. Countless petitions and protest demonstrations that were held in the major capitals of the world have ended in deaf ears. The response by the government has been more repression and more violence. Today there is no independent media in the country due to the wide spread practice of jailing and forcing publishers and reporters in to exile. Today there are no functioning independent political parties due to the practice of systematic disruption of their normal day-to-day activities, jailing of opposition leaders or forcing them out of their country. Currently, prisons are filled with thousands of well-known political, civic organization and religious leaders as well as journalists under trumped-up “terrorism” charges. Certain ethnic groups are targeted. These prisoners are tortured to confess and to corroborate the charges against themselves and their colleagues. In spite of this massive oppression, victims of the regime have no recourse to justice since the judiciary is made subservient to the political manipulation of the ruling party.

As presented above, Ethiopians are once again faced with a regime that is led by a group of people who oppress them in multiple ways; deny them basic human rights and are hell-bent on blocking the democratic process for self-rule. We are also aware that though the regime comes from Tigrai, a thousands of Ethiopians that come from this ethnic group are victimized and have already started armed insurrection well over one decade ago. The predicament the Ethiopian people find themselves in currently is not unique. Under similar conditions, the founding fathers of one of the earliest democracies in the world have said it best in the Declaration of Independence by the Colonies from the Great Britain: ‘We hold these truths to be self-evident, that all men are created equal, that they are endowed by their Creator with certain unalienable Rights, that among these are Life, Liberty and the pursuit of Happiness. — That to secure these rights, Governments are instituted among Men, deriving their just powers from the consent of the governed, — That whenever any Form of Government becomes destructive of these ends, it is the Right of the People to alter or to abolish it, and to institute new Government, laying its foundation on such principles and organizing its powers in such form, as to them shall seem most likely to affect their Safety and Happiness’ A similar spirited paragraph is found in the preamble of African National Congress’s Freedom Charter. These words ring true today for the people of Ethiopia.

At this critical juncture, to facilitate the Ethiopian people’s struggle with able leadership, the democratic forces in the country are coalescing under the newly formed UMSED as a “broad church”.. It is not lost on the part of these democratic forces that one of the potential obstacles on the road to the Ethiopian people’s struggle for freedom and democracy is the international community’s multifaceted collaboration with the TPLF dominated government with seeming indifference to the prevailing repressive political conditions in the country.

Following their new goal of making inroads into Africa, some countries have become major financiers of the TPLF repressive regime. This may be an expected behavior from these governments, given the nature of their systems. However, the West’s support for the rogue dictatorial regime is inconsistent with the values of freedom, justice, and democracy the West practices at home and espouses for the stable world order. The West led by the US has correctly and understandably declared terrorism as the number one menace to global peace while in a typical short-term calculus have also decided to consider dictatorial regimes like that of Ethiopia to be “allies” in its anti-terrorism effort and the disorder in the Greater Horn of Africa region. As a result, the West has made the Ethiopian regime a beneficiary of its substantial financial, political, diplomatic and even military support indirectly emboldening it to continue with impunity in its human rights abuse and repression of its own people. This policy on the part of the Western countries is not only short sighted and immoral but is more than likely to lead to greater instability especially when minority regimes collapse.

It is obvious that the repressive nature of the regime and its extensive human rights abuses are among the main causes of instability in the region. For all those who are willing to see the writing on the wall, the regime is internally in continuous conflict with its citizens; it uses scorch-earth military expeditions in the Ogaden region to the east and makes occasional incursions into Kenyan territory pursuing armed resisters. The regime is also locked in constant conflict with Eritrea in the north. This is the reason why the regime has one of the biggest standing army in Sub-Saharan Africa thus spending large portion of the poor country’s budget on the military while the danger of famine and lack of resources for basic needs of its population is always lurking around.

While this is the true reason for the TPLF regime to build an army that is beyond the country’s legitimate external security threat need, it cynically uses a fraction of this army in international peace keeping missions in order to get acquiescence from the West for its nefarious repression at home as well as use these missions as a source of hard currency income for its corrupt highest military brass. Recently, the Ethiopian government is even seen scheming to leverage its security cooperation with the West, hopefully in vain, for extending its repressive hand abroad by invoking the legitimate rebellion and resistance of Ethiopians as a terrorist act. The truth is that the Ethiopian people’s resistance is a very disciplined and well organized struggle that is focused only on a political goal of making Ethiopia a democratic country either by forcing the minority regime to come to table or removing it if it continues to persist on blocking Ethiopians’ right for self-government. The people’s resistance movement is also very much aware of its responsibilities for the Ethiopian people, the people of the region and the international community. It is a resistance movement which is informed from the rich tradition of Ethiopian history. It is not a group of bandits and terrorists. It includes several members of the opposition who contested the ill-fated 2005 election. In deed it is a democratic force and represents a cross section of Ethiopians.

In their long history of existence, Ethiopians have shown no affinity for internalizing any sort of extremist ideology let alone to terrorist practice despite the persistent attempt to impose communism during the military regime and ethno-centric politics by the current regime on them. The history of Ethiopia is replete with building good relationship with its neighbors, peaceful coexistence and social stability. Ethiopian history also shows the courage and willingness of the people to lay their lives and honor to resist and prevail over colonialism and minority rule.. Witness the Ethiopian people’s glorious victory in the battle of Adwa and their resistance against fascist Italy even when the world turned its face and gave them its cold shoulders.

To stay true to our forefathers’ tradition saying no to oppression and its own commitment for democracy, UMSED pledges to work hard and to pay the necessary sacrifice to put an end to the tyranny of TPLF dominated regime and to assure that the TPLF regime becomes the last dictatorship in Ethiopian history. The UMSED appeals to the peace loving people of the world and the international community to stand in solidarity with the Ethiopian people; for it is only by democratizing Ethiopia that a lasting stability can be achieved and the specter of terrorism can be dealt with effectively in one of the most volatile regions of the world. Anything else will further destabilize Ethiopia and turns the Horn of Africa into a hot bed of terrorism.

From the Foreign Relations Office of United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED)

September 25, 2015

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!

$
0
0

def-thumb“የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኔ እኮራለሁ” እያሉ በአገዛዙ የይስሙላ ችሎት ሳይቀር በድፍረት የሚናገሩ ወጣቶች ተፈጥረዋል። ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለሀገር አንድነት መስዋዕትነት መክፈል የሚያኮራ ተግባር መሆኑ በተግባር የሚያሳዩ ወጣቶች መጥተዋል፤ አሁን በርካቶችም እየመጡ ነው። ወያኔ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በማኅበረሰባችን ውስጥ የዘራው የፍርሀትና የአድርባይነት ስሜት በራሱ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ተወልደው ባደጉ ወጣቶች እየተናደ፤ በምትኩ ሊጠፋ ተቃርቦ የነበረው የአገር ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እያንሰራራ ነው።

ቅንነት፣ ሀቀኝነት እና ጽናት ከተጣሉበት ጉድጓድ አቧራቸውን አራግፈው እየተነሱ ነው። በማኅበረሰባች ውስጥ ትልቅ የስነልቦና አብዮት እየተካሄደ ነው።

ከስነልቦና ለውጡ ጋርም በተግባር የአገር አድን ሠራዊትን የመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው። ወጣቶች የአገራቸው ባለቤት መሆናቸው ተገንዝበው የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት መነሳታቸው ተስፋ ሰጪ ነገር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ የለውጥ ወቅት ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አጽንዖት ልንሰጣቸው ስለሚገቡ የድርጅትና የሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) አስፈላጊነት ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና በተግባርም መተርጎም አስፈላጊ ነው ብሎ ያምናል።

ወጣቶች ትግሉን ለመቀላቀል መሻታቸው መልካም ነገር ነው። ሆኖም ግን በድንገት ብድግ ብለው መንገድ ከመጀመር ይልቅ ከሚያምኗቸው ወዳጆቻቸው ጋር የመሠረቱት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋርም ትስስር የፈጠረ ስብስብ አካል ሆነው መቆየታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው።
በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ የሚስጢር ድርጅት ማዋቀር አስቸጋሪ መሆኑ የማያጠራጥር ቢሆንም የማይቻል ነገር ግን አይደለም። ወጣቶቻችን በአምባገነን ሥርዓት ውስጥም ሆነው በዲሲፕሊን የታነፀ ድርጅት የመፍጠርን ክህሎት መላበስ ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ስንችል ነው የህወሓትን ፀረ-አገርና ፀረ-ትውልድ ተግባር ማክሸፍ የምንችለው። ትግሉን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ማቀጣጠል የምንችለው በየአካባቢው የተደራጀ የለውጥ ኃይል ሲኖረን ነው። ስለሆነም የምስጢር የተደራጀ አካል በየመኖሪያና የሥራ አካባቢዎቻችን ሁሉ እንዲኖር ማድረግ ከአጣዳፊ ሥራዎቻችን አንዱ እናድርገው።

ሁለተኛው ነጥብ ሥነሥርዓትን የሚመለከት ነው። ሥነሥርዓት ከሌለ ድርጅት የለም። የህወሓት አገዛዝ ያሳደረብን ጎጂ የባህል ተጽዕኖ ከባድ በመሆኑ ራሳችንን በሥነሥርዓት ለማነጽ መልፋት ይጠበቅብናል። አገራችንና ራሳችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ አውጥተን የተሻለ ሥርዓት ማምጣት የምንችለው ራሳችን፣ ድርጅታችን እና ተግባሮቻችን ለሥነሥርዓት ተገዢ ስናደርግ ነው። የነፃነት ታጋዮች ራሳቸውን ለሥነ ሥርዓት ያስገዙ መሆን ይኖርባቸዋል። አስተሳሰባችን ራሱ ሥነ ሥርዓት የያዘ ሊሆን ይገባዋል። እንደዚሁም ሁሉ ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት የታነጹ ሊሆኑ ይገባል።

የንቅናቄዓችንን መዋቅር በመላው አገራችን ከዘረጋን፤ ራሳችንን፣ አስተሳሰቦቻችንና ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት ከመራን፤ ቅንነት፣ ሀቀኝነትና ጽናት ከተላበስን ድላችን ቅርብ እና አስተማማኝ ነው። ለውጥን የሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ይተግብር።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Viewing all 39 articles
Browse latest View live